ጉዳዩ መልስ ለመቀበል በተቀጠረ ቀን የከሣሽ አአለመቅረብ ስለሚኖረው ውጤት (ሼህ ኢኢትዮጵያ A/ማ እእና አአስቴር ብርሃነስላሴ) ................................... 6A
No summary available.
የካቲት 11 ቀን 1995 ዓ.ም የሰጠው ፍርድ ፀንቷል። ይጻፍ።
ለፍድራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የመ/ ዳኞች፡- አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍሰሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወ/ሮ ስንዱ አለሙ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አመልካቶች፡- ሼል ኢትዮጵያ A/ማ መልስ ሰጪ፡- ወ/ሮ አስቴር ብርሃነ ስላሴ በከሣሽነት ወይም በተከሣሽነት የሙግት ተካፋይ ስለመሆን
59 60
ተከሣሽ ከክሱ አስወጥቶ /Ex-parte/ ጉዳዩ መታየቱ የሚቀጥለው ተከሣሹ ጉዳዩ ላሰማ በተቀጠረበት ቀን ችሎት ያልቀረበ እንደሆነ ነው።
ጉዳዩ የተከሣሽን መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ቀን ተከሣሽ ያልቀረበ እንደሆነ መልሱን በጽሁፍ ከማቅረብ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጥቅሞች ይቀረቡታል እንጂ በቀጣዩ ሂደት ከመሳተፍ አይከለከልም።
ሐምል 29 ቀን 1997 የመ/ ዳኞች፡- አቶ መንበረፀሐይ ታደሰ አቶ ፍሰሐ ወርቅነህ አቶ አብዱልቃድር መሐመድ ወ/ሮ ስንዱ አለሙ አቶ መስፍን እቁበዮናስ አመልካቶች፡- ሼል ኢትዮጵያ አክስዮን ማህበር መልስ ሰጪ፡- ወ/ሮ አስቴር ብርሃነ ስላሴ
በዚህ መሰረት ለቀረበው ክርክር መነሻ የሆነው የፍድራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የሰጠውና የጠቅላይ ፍ/ቤት የተቀበለው ትእዛዝ ነው።
የአሁኑ አመልካች ሁለቱም ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሣኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በማለት የሰበር ማመልከቻ ያቀረበ ሲሆን ጉዳዩ በሰበር መታየት ይገባዋል ተብሎ በመታዘዙ መልስ ሰጪም ቀርቦ በጉዳዩ ላይ የጽሁፍ ክርክሩን አቅርቦአል።
የአመልካች አቤቱታ ከፍተኛ ፍ/ቤት የከሣሽ ክስ እንዲሻሻል ትእዛዝ መስጠቱን አውቆ ለተሻሻለው ክስ መልስ እንዲያቀርብ ሲጠይቅ ፍ/ቤቱ ቀደም ሲል በፍ.ብ.ሥ.ሥ.ሕ.ቁ 73 መሰረት ጉዳዩ አመልካች በልለበት እንዲታይ የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ የአመልካችን ጥያቄ ውድቅ በማድረጉ የሥነ ሥርዓት ሕጉን የጣሰ አሰራር ነው በማለት በሰበር እንዲስተካከልለት አመልክቷል። የአመልካች ዋና ክርክር የተሻሻለው ክስ እንደ አዲስ ክስ መቆጠር ስላለበት ቀደም ብሎ ክርክሩ በልለበት እንዲታይ የተወሰነ ቢሆንም ለተሻሻለው ክስ መልስ የመስጠት መብቱ ላቀርበት አይገባም የሚል ነው። መልስ ሰጪ በዚህ ጉዳይ ላይ መለሱን በጽሁፍ በማቅረብ የክሱ መሻሻል ቀደም ሲል የተሰጡትን ትእዛዞች የሚሽር ባለመሆኑ አመልካች ለተሻሻለው ክስ መልስ ለማቅረብ ያቀረበው ጥያቄ በሁለቱም ፍቤቶች ውድቅ መደረጉ የሕግ ስህተት መኖሩን አያሳይም በማለት ተከራክሯል።
ይህ የሰበር ችሎት በዚህ ጉዳይ ላይ አመልካች መልስ ለማቅረብ በተቀጠረበት ቀን መልሱን ይዞ ባለመቅረቡ ጉዳዩ በልለበት እንዲታይ መታዘዙን 6261 ተገንዝቧል፣ በተሻሻለው ክስ መልስ ላያቀርብ አይገባም የሚል ትእዛዝ የተሰጠውም ቀደም ብሎ የተሰጠውን ትእዛዝ መሰረት በማድረግ እንደሆነ ተረድቷል። በዚህም መሰት ጉዳዩን በአግባቡ ለማስተናገድ የአሁኑ አመልካች መልስ እንዲያቀርብ በተቀጠረበት እለት መለሱን ይዞ ባለመቅረቡ የሚከተለው ሕጋዊ ውጤት ምንድነው?
የሚለውንና ተያያዥነት ያላቸውን ልሎች ነጥቦች መመርመር ተገቢ ሆኖ አግኝቶታል።
አንድ ተከሣሽ ጉዳዩ ለመልስ በተቀጠረበት እለት መልሱን ይዞ ካልቀረበ ክርክሩ በልለበት የሚሰማ መሆኑ ፍርድ ቤቱ በሚልክለት መጥሪያ ላይ እንደሚገልጽለት በፍሥ.ሥ.ሕ.ቁ 233 ላይ ተደንግጓል። በልላ በኩል የፍ.ሥ.ሥ.ሕ.ቀ 70 ክርክሩ እንዲሰማ በተወሰነው ቀነ ቀጠሮ ከሣሽ ቀርቦ ተከሣሽ ያልቀረበ እንደሆነ ተከሣሹ ያልቀረበው የተላከለት መጥሪያ ደርሶት ከሆነ ተከሣሹ በልለበት የነገሩ መሰማት እንደሚቀጥል ይደነግጋል። አነዚህ ሁለት ድንጋጌዎች ሁለት በተለያዩ ጊዜ የሚከናወኑ የሙግት ደረጃዎችን የሚመለከቱ ቢሆኑም የተከሣሽን መቅረት አስመልከቶ የሚያስከትሉት ውጤት ተመሳሳይ ይመስላል። የጽሁፍ መልሱን ሳያቀርብ የቀረ ተከሣሽ በ233 መሰረት በልለበት ጉዳዩ እንደሚሰማ ጉዳዩ ለመስማት በተቀጠረበት ቀን ያልቀረበ ተከሣሽም በተመሳሳይ ሁኔታ ጉዳዩ በልለበት እንደሚሰማ በቁጥር 70(ሀ) መሰረት ትእዛዝ የሚሰጥበት ይመስላል። የሁለቱም ድንጋጌዎች የአማርኛ ቅጂ ለመልስ በተቀጠረበት ቀን መቅረትና ጉዳዩ እንዲሰማ በተቀጠረበት ቀን መቅረት አንድ አይነት ውጤት ያላቸው እንደሆነ የሚገልጹ ቢሆኑም የሁለቱም የእንግላዝኛ ቅጂዎች ግን የተለየ ጽንሰ ሃሳብ የሚያስተላልñ ናቸው።
የእንግላዝኛ የ70(ሀ) የእንግላዝኛ ድንጋጌ ስለ Ex-part ሲናገር የ233 ግን የሚደነግገው ስለ default proceeding ነው።ሁለቱም የተለያየ ይዘት የተለያየ ውጤት ያላቸው ናቸው።
የ70(ሀ) የእንግላዝኛ ቅጂ 70 where the plaintiff appears and defendant does not appear when the suit is called on for hearing (a) if it is proved that the summons was duly served, the suit shall be heard ex-parte በማለት ሲደነግግ አግባብነት ያለው የ233 ክፈል ደግሞ …. The court shall cause… requiring him to appear with his statement of defense to be fixed in the summons and informing him that the case wile be proceeded withnotwithstanding that he does not appear or that he appears without his statement of defense. በማለት ይደገግጋል።
ሁለቱን የአንግላዝኛ ቅጂዎች በማነጻጸር ለመገንዘብ እንደሚቻለው ለመልስ በተቀጠረ ቀን ተከሣሽ መልሱን ይዞ ባይቀርብ የሚከተለው ውጤት ለመስማት በተቀጠረበት ቀን ባይገኝ ከሚከተለው ውጤት ጋር አንድ አይነት አይደለም። የ233 ድንጋጌ መለሱን ባያቀርብም የጉዳዩ መሰማት እንደሚቀጥል (default proceeding) ከሚይሳይ በቀር ተከሣሽ ከክርክር እንዲወጣ የሚያደርግበት ሥርዓት አለመኖሩን ያሳያል። በልላ በኩል በ70(ሀ) ስር ያለው ድንጋጌ ጉዳዩ ለመሰማት በተቀጠረበት ቀን የቀረ ተከሣሽ ጉዳዩ አሱ በልለበት መቀጠል(default proceeding) ብቻ ሳይሆን ከክርክሩ እንዲወጣ (ex-part) እንደሚደረግ በግልጽ ያስቀምጣል። ይህም በአማርኛ ቅጂ ላይ ያለው አገላለጽ በእንግላዝኛው ላይ ያለውን ሃሳብ በትክክል አለማስተላለñን ያመለክታል።
የትርጉም ልዩነት ሲኖር የአማርኛውን ቅጂ በመውሰድ እልባት መስጠት ይቻላል በማለት ጉዳዩ ማጠቃለል አንዱ አማራጭ ነው። ሆኖም ይህ አማራጭ አሁን በያዝነው ጉዳይ በግልጽ የሚታየውን የትርጉም ስህተት እንዲቀጥል የሚያደርግ በመሆኑ ትክክለኛ አማራጭ ነው አንልም። ይልቁም የተከሰተውን የትርጉም ልዩነት ከአጠቃላይ የሕጉ ዓላማ እንዲሁም ተከሣሽ በቀረበበት ክስ የመደመጥ መብትን ይበልጥ ላያስከብር በሚችል ሁኔታ መተርጐም በበለጠ የፍትህ አስተዳደርን ዓላማ በበለጠ ስለሚያሳካ የእንግላዝኛው ቅጂ መከተሉን መርጠናል።
በዚህም መሰረት አንድ ተከሣሽ ከክስ እንዲወጣ መደረግ ያለበት ጉዳዩ እንዲሰማ በተቀጠረበት ቀነ ቀጠሮ ሳይቀርብ የቀረ እንደሆነ እንጂ መልስ ለመቀበል ቀጠሮ በተያዘበት እለት ካልቀረበ መሆን የለበትም። ይህ አተረጓጐም ተከሣሹ መልስ ለመቀበል በተያዘ ቀጠሮ ሳይቀርብ ቢቀር ፍርድ ቤቱ ምን ያደርጋል የሚል ጥያቄ ማስከተሉ የሚቀር አይደለም። ይህን ጥያቄ ለመመለስ ፍርድ ቤት የሰጠው ቀጠሮ ሳይከበር ቢቀር ፍርድ ቤቱ ምን ያደርጋል ከሚል ልላ ጥያቄ ጋር ተያይዞ መመለስ ያለበት ነው።
በሙግት ሂደት ፍርድ ቤት የተለያዩ ጉዳዮች መከናወናቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ቀጠሮዎችን ይሰጣል ሆኖም ፍ/ቤቱ የሰጠው ቀጠሮ በአንዱ ወይም በልላው ተሟጋች በተሰተጓጎለ ቁጥር ለመስተጓጎሉ ምክንያት የሆነው ወገን ከክርክ እንዲወጣ (Ex-parte) አይደረግም። የቀጠሮው አለመከበር ቀጠሮ ከተሰጠሰት ምክንያት ተነጥሎ የሚታይ ባለመሆኑ በየጉዳዩ የተለያየ ትእዛዝ የሚሰ ቢሆንም መሰረታዊው የጉዳዩ ሂደት የሚስተናገደው በሥነ ሥርዓት ሕግ ምእራፍ 7 በሚገኙት መርሆዎችና ድንጋጌዎች መሰረት መሆን አለበት። በፍ.ሥ.ሥ.ሕ.ቁ 194 እንደተገለፀው በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ መከናወን ያለበት ድርጊት በተወሰነው ጊዜ ውስጥ ካልተከናወነ ዋጋ እንደልለው የገልጻል። በዚህም መሰረት በተወሰነ ጊዜ ውስጥ መልሱን እንዲያቀርብ የታዘዘ ተከሣሽ መልሱን ከማቅረብ ጋር ተያየዘው የሚነሱ ጥቅሞች ይቀሩበታል።
በቀጣዩ ሂደት ከመሳተፍ አይከለክልም።
63 64 ወደያዝነው ጉዳይ ስንመለስ አሁን አመልካች በተሻሻለው ክስ ላይ መልስ መስጠት አትችልም የተባለው ቀደም ብሎ ጉዳዩ መልስ ለመቀበል በተቀጠረበት ቀን መለሱን ይዞ አለመቅረቡን ምክንያት በማድረግ ነው። ሆኖም ጉዳዩ ለመልስ በተቀጠረ ቀን ተከሣሹ መልሱን ሳያቀርብ ቢቀር የጽሁፍ መልስና የማስረጃ ዝርዝር የማቅረብ እድሉን ከሚያጣ በቀር ከክርክሩ ውጪ እንዲሆን መታዘዝ አልነበረበትም።
በዚህም ምክንያት አንድን ተከሣሽ ሕጉ ከሚፈቅደው ሁኔታ ውጪ ከክርክር ውጪ ማድረግ በጉዳዩ ላይ የሥነ ሥርዓት ግድፈት መፈጸሙን ያመለክታል። ክሱ እንዲሻሻል ትእዛዝ ሲሰጥ ተከሣሸ መልስ ማቅረብ አትችልም የተባለው ከዚህ ሥነ ሥርዓት ግድፈት ጋር በተያያዘ ምክንያት ነው። አመልካቹ ከክርክሩ መውጣት ሳይኖርበት አውጥቶ ለተሻሻለው ክስ መለስ አታቀርብም መባሉ አግባብ አይደለም።
የጠቅላይ ፍ/ቤት የሥነ ሥርዓት ግድፈት መፈጸሙን በማመን ይህን ግድፈት ማስተካከል ሲገባው አልፎታል። በመሆኑም የሰበር ችሎት የተፈፀመውን የሥነ ሥርዓት ግድፈት በፍ.ሥ.ሥ.ሕግ ቁጥር 211 ስር በተደነገገው መሰረት ማሰተካከል አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል።
ውሣኔ
የአሁን አመልካች በከፈተኛ ፍ/ቤት በነበረው ክርክር ከክርክር ውጪ የተደረገው በአግባሱ ስላልሆነ ወደ ክርክሩ ይግባ።
ለተሻሻለው ክስ መልስ ማቅረብ እንዲችል በከፍተኛው ፍ/ቤት የተሻሻለው ክስ ግልባጭ ይሰጠው።
ወጪና ኪሣራ የየራሳቸውን ይቻሉ።
ለፍድራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት