የአንድ ክስ ዝርዝር ይዘቱ ሳይታይ እርስቱ ብቻ ታይቶ የፍርድ ቤት የሥረ ነገር ዲኝነት የሚወሰንበት የሕግ አግባብ የላለ ስለመሆኑ ስልጣን ሳይኖር የተሰጠ ውሳኔ ስርዓቱን ጠብቆ አቤቱታ እስከቀረበበት ድረስ ሉፀና የማይገባው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 9 እና 231(ለ) VIII
No summary available.
ሐምል 14 ቀን 2007 ዓ.ም ዳኞች፡- አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ ተኽሉት ይመሰል እንዲሻው አዲነ ቀነዓ ቂጣታ አመልካች፡- ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዲ 4 አስተዲደር ፅ/ቤት - የቀረበ የለም ተጠሪ፡- ወ/ሮ አሰለፈች ወልዳ - ጠበቃ ሙለጌታ ደላ ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቶአል።
ጉዲዩ የመንግስት የንግድ ቤት የተከራይነት መብትን የሚመለከት ክርክር ነው። ክርክሩ የተጀመረው የአሁኗ ተጠሪ ባሁኑ አመልካች ላይ በመሰረቱት ክስ መነሻ ነው።ተጠሪ በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በ3/03/2005 ዓ.ም በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ፡- ተጠሪ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዲ 4 ክልል ውስጥ የሚገኘውን ቁጥሩ 123 የሆነውን የንግድ ቤት ከአመልካች ተከራይተውና በቤቱ ላይ የንግድ ፈቃድ አውጥተው ይነግደ ከነበሩት ከወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ ገርቢ ተከራይተው ክስ እስከአቀረበቡት ጊዜ ድረስ ሲነግደበት የነበረ መሆኑን፣በመመሪያ ቁጥር 4/2004 መሰረት ተጠሪ ተጠቃሚ መሆናቸውን፣ሆኖም የአሁኑ አመልካች ተጠሪን የመመሪያው ተጠቃሚ መሆናቸውን እየገለፀ ሲያመላልሳቸው ከቆየ በኋላ ሕዲር 01 ቀን 2005 ዓ/ም በተፃፈ ማስጠንቀቂያ የቤቱን የተከራይነት መብት ለተጠሪ ማከራየት እንደማይችል በመግለፅ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ቤቱን እንድታስረክቢ በማለት ያሳወቃቸው መሆኑን፣ከአመልካች ጋር የኪራይ ውል አድርገው የነበሩት ግለሰብ አመልካችን ሳያሳውቁ ለሶስተኛ ወገን ቤቱን አከራይተው መገኘታቸው ተጠሪን በመመሪያው መሰረት ተጠቃሚ የሚያደርጋቸውና አመልካችም ከተጠሪ ጋር በመመሪያው መሰረት ውል የመዋዋል ግዳታ ያለበት መሆኑን፣በመመሪያው መሰረት አመልካች ከተጠሪ ጋር የኪራይ ውል የመዋዋል ግዳታ እያለበት ቤቱን አስረክቢ በማለት የገለጸላቸው የሁከት ተግባር መሆኑን ዘርዝረው የተፈጠረው ሁከት ተወግድላቸው አመልካች ከተጠሪ ጋር በመመሪያው መሰረት ውል እንዱዋዋል ይወሰንላቸው ዘንድ ዲኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው። የአሁኑ አመልካች ለክሱ በሰጠው መልስም አከራካሪው ቤት አብነ ቡድን ለተባለ የጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅት የተሰጠ እንጂ ተጠሪ መብትና ጥቅም የላላቸው መሆኑንና የአመልካች ተግባር ሁከት ነው ልባል የማይችል መሆኑን በመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያነት ያቀረበ ሲሆን በፍሬ ነገር ደረጃ ደግሞ አመልካች ቤቱን ለፈለገው ሰው የማከራየት መብት ያለው መሆኑን፣የአብነ ጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅት አባል የነበሩት ወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ የተባለ የማህበሩ አባል የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የተቋቋሙበትን ዓላማ በሚፃረር መልኩ ለተጠሪ አስተላለፈው የተገኙ በመሆኑ ቀድሞውኑም ባልነበራቸው መብት ሉሰሩበት የሚችለበት አግባብ የለም የሚለትን ምክንያቶችን ዘርዝሮ ክሱ ውድቅ ላሆን ይገባል ሲል ተከራክሯል።
ጉዲዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤትም በአመልካች በኩል የቀረበውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አልፍ ፍሬ ነገሩን በተመለከተ ደግሞ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተጠሪ ቤቱን ከአመልካች እውቅና ውጪ ከወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ ተከራይተው ሲሰሩበት የነበረ መሆኑ መረጋገጡንና መመሪያው ደግሞ በዚህ አግባብ የመንግስት ቤትን ተከራይቶ ሲሰራ የነበረ የተከራይ ተከራይ ተጠቃሚ እንደሚሆን የደነገገ መሆኑን በምክንያትነት ይዞ አመልካች የሁከት ተግባር ፈፅሟል፣ሁከቱ ሉወገድ ይገባል በማለት ወስኗል። በዚህ ውሳኔ የአሁኗ አመልካች ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለፋዳራለ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦ ግራ ቀኙ ከተከራከሩ በኋላ ፍርድ ቤቱ ጉዲዩን መርምሮ የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ ሙለ በሙለ አፅንቶታል። አሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንኑ ውሳኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው። የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም፡- የስር ፍርድ ቤቶች የአመልካች ተግባር የሁከት ተግባር ነው በማለት መወሰናቸው የአመልካችን ቤት ለፈለገው ሰው የማከራየት መብቱን ያላገናዘበና ቤቱ ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ተሰጥቶ እነዚህ ድርጅቶች ወደ መካከለኛ ደረጃ ሲተላለፈ በልላ ተቋም አግባብነት ባለው መመሪያ መሰረት የሚተላለፍ ሁኖ እያለ ይህ ታልፍ ለጉዲዩ አግባብነት የላለው መመሪያ መሰረት ተደርጎ የተጠሪ የተከራይነት ተጠቃሚነት ሉረጋገጥላቸው ይገባል ተብል መወሰኑ ያላግባብ ነው የሚል ነው።አቤቱታው ተመርምሮም በዚህ ችልት እንዱታይ በመደረጉ ተጠሪ ቀርበው ግራ ቀኙ በፅሐፍ እንዱከራከሩ ተደርጓል።
የጉዲዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን እኛም፡-ክስ የቀረበበት ጉዲይ የሚወድቀው በፋደራል ፍርድ ቤቶች ነው? ወይስ በአዱስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ስር ነው? የሚለውን ነጥብ መሰረት በማድረግ አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት መሆን አለመሆኑን መርምረናል።
በዚህም አመልካች የሁከት ተግባር ፈጥሮብኛል በማለት ተጠሪ የሚከራከሩት ተጠሪ አከራካሪውን የንግድ ቤት የአመልካች ተከራይ ከሆኑት ከወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ ተከራይተው በመሰራት ላይ እያለ መመሪያ ቁጥር 4/2004 መውጣቱንና በዚህም ምክንያት የተከራይነት መብት ተጠቃሚ መሆን የሚችለት ተጠሪ ሁነው እያለ አመልካች ተጠሪን ቤቱን ለቀው እንዱያስረክቡ በማለት ማስጠንቀቂያ መፃፈ የሁከት ተግባር በመሆኑ ሁከቱ ሉወገድ ይገባል፣የመመሪያው ተጠቃሚነትም ሉረጋገጥልኝ ይገባል በማለት ሲሆን የበታች ፍርድ ቤቶችም የግራ ቀኙን ክርክር መርምረው የአከራካሪው ቤት ተከራይ ማን እንደሆነ፣ ወደ ተጠሪ ይዞታ የገባበት አግባብ ምን እንደሆነ፣ተጠሪ ቤቱን የተከራዩበት አግባብ ከአመልካች እውቅና መሆኑ፣በዚህ አግባብ የተላለፈ የንግድ ቤት የተከራይነት መብት ተጠቃሚ የሚሆነው ደግሞ የተከራይ ተከራይ ስለመሆኑ በመመሪያ ቁጥር 4/2004 አንቀጽ 6 ስር መመልከቱን መሰረት በማድረግ የአመልካችን ተግባር ሁከት ነው በማለት መወሰናቸውን ከክርክሩ ሂደት ተገንዝበናል።
ከዚህም መረዲት የሚቻለው የተጠሪ የዲኝነት ጥያቄ በቀጥታ ከመመሪያ ቁጥር 4/2004 አፈጻጻም ጋር የተያያዘ መሆኑን ነው። ተጠሪ የአመልካች ነበር በተባለው የንግድ ሱቅ የገቡት አመልካች እንደሚከራከሩት በቤቱ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት በተመደበበት ነው? ወይስ የንግድ ቤቱ ለጥቃቅን አነስተኛ ተቋማት አገልግልት ከተመደበበት አላማ ውጪ ወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ ወይም የእብነ ቡድን አባላት በመከራየታቸው ነው?የሚለው አከራካሪ ጭብጥ ጭምር ከመመሪያው አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የሚታይ እና ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ተመርምሮ ውሳኔ የሚሰጥበት ነው። አመልካችም ሆነ ተጠሪ ግንኙነቱ የንግድ መደብር ኪራይን መሰረት ያደረገ ነው የሚል ክርክርም የላቸውም። የንግድ ቤቱ ተከራይ ከነበሩት ከወ/ሮ ብርቅነሽ ሸዋረጋ ከአብነ ቡድን አባለት እና ከተጠሪ መካከል በመመሪያ ቁጥር 4/2004 መሰረት የተከራይነት መብት ሉያገኝ የሚገባው ማነው? የሚለው ጥያቄ በመሰረቱ በመመሪያው ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት አድርጎ ምላሽ የሚያገኝ የመመሪያ አፈጻጸም ጉዲይ ከሚሆን ውጪ ከሁከት ድርጊት ጋር ግንኙነት ያለው ጉዲይ አይደለም። የአንድ ክስ ዝርዝር ይዘቱ ሳይታይ እርስቱ ብቻ ታይቶ የፍርድ ቤት የሥረ ነገር ዲኝነት የሚወሰንበት የሕግ አግባብ የላለ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በጉዲዩ ላይ የሥረ ነገር ዲኝነት ያለው መሆን ያለመሆኑን ተከራካሪ ወገን ባያነሳውም ራሱ ማረጋገጥ ያለበት መሆኑን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ//ቁጥር 9 እና 231(ለ) ድንጋጌዎች ይዘት የምንገነዘበው ጉዲይ ነው። በመሆኑም የተጠሪ ክስ እርስቱ የሁከት ይወገድልኝ የሚል ቢሆንም ዝርዝር ይዘቱ ከመመሪያ ቁጥር 4/2004 አፈጻጸም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ሲሆን መመሪያውን የሚያስፈጽሙት ደግሞ እንደ አመልካች ያለት የከተማው አስፈጻሚ አካላት ናቸው።
መመሪያውን መሰረት አድርጎ የሚነሳ የንግድ ቤት የተከራይነት መብት ጥያቄ ከከተማው አስተዲደር አስፈጻሚ አካላት የመቆጣጠር ስልጣን እና ተግባር ጋር እንዱሁም የከተማው አስተዲደር ከሚያስተዲድራቸው የመንግስት ቤቶች ጋር የተያያዘ እስከሆነ እና የከተማው አስተዲደር አካልም በተከሳሽነት የተሰየመ እስከሆነ ድረስ ደግሞ የዚህ ዓይነት ጉዲዮችን ተቀብል የማስተናገድ የስረ ነገር ስልጣን የከተማው ፍርድ ቤቶች ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 361/1995 በተሻሻለው የአዱስ አበባ ከተማ ቻርተር በአንቀጽ 41(1) (ለ) እና (ረ) ስር በግልጽ የተመለከተ በመሆኑ የዚህ ዓይነቱ ክስ የሁከት ስም ተሰጥቶት በመቅረቡ ብቻ በፋዳራል ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ስር ሉወድቅ የሚችልበት የህግ አግባብ አይኖርም።
በመሆኑም ክስ የቀረበበት ጉዲይ የሚወድቀው በፋደራል ፍርድ ቤቶች ሳይሆን በአዱስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ስልጣን ስር ሁኖ እያለ የፋዳራለ መጀመሪያ ደረጃ ጉዲዩን አይቶ ዲኝነት መስጠቱ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ያለበት በመሆኑና ስልጣን ሳይኖር የተሰጠ ውሳኔ ደግሞ ስርዓቱን ጠብቆ አቤቱታ እስከቀረበበት ድረስ ሉፀና የማይገባው በመሆኑ ተከታዩን ወስነናል።
ተሰጥቶ በፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ በ02/08/2006 ዓ.ም የጸናው ውሳኔ በፍትሐብሕር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 348(1) መሰረት ተሽሯል።
No topics extracted.