አንድ ሰራተኛ ለአሰሪው በሥራ ክርክር ምክንያት ያወጣውን ወጭና ኪሳራ የመክፈል ግዳታ የሚጣልበት በክርክሩ ተረች በመሆኑ ምክንያት ብቻ ሳይሆን ሰራተኛው በአሰሪው ላይ ያቀረበው ክስ ሀሰተኛና በተጭበረበረ ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ስለመሆኑ የፍትሐ ብሓር ሥነ ስርዓት ህግ ቁጥር 463 ፣465 (1) አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 161
No summary available.
ሐምል 29 ቀን 2007 ዓ.ም ዳኞች፡- አልማው ወላ ዓሉ መሀመድ ተኽሉት ይመሰል አዲነ እንደሻው ቀነዓ ቂጤታ አመልካች፡- አቶ ጌትነት ከበደ - ቀረቡ ተጠሪዎች፡- ሃያት ሜድካል ከላጅ አልቀረቡም።
መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል።
ጉዲዩ የቀረበው የአመልካች የጠበቃ አበልና ወጭና ኪሳራ ብር 6000/ስድስት ሺ ብር/ እንዱከፍል የተሰጠው ውሳኔ በአግባቡ ነው ወይስ አይደለም? የሚለውን ጭብጥ አጣርቶ ለመወሰን ነው። ጉዲዩን እንደመረመርነው አመልካች የስራ ውለ ከህግ አግባብ ውጭ ተቋርጧል የሚል ክስ በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቅርቦ፣ተጠሪ የአመልካች የስራ ውል የተቋረጠው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዲይ አዋጅ በሚደነግገው መሰረት መሆኑን ገልጾ በመከራከሩ፣ የስር ፍ/ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኃላ ተጠሪ የአመልካችን የስራ ውል ያቋረጠው በህግ አግባብ ነው በማለት አመልካች /ከሳሽ/ ለተጠሪ ለተከሳሽ የጠበቃ አበል ብር 5000 / አምስት ሺ ብር/ እና ኪሳራ ብር 1000 /አንድ ሺ ብር/ በድምሩ ብር 6000 /ስድስት ሺ ብር/ ይክፈል ማለት ውሳኔ ሰጥቷል።
አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ በፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ይግባኝ አቅርቧል። የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ /ተጠሪ/ ለአመልካች የሁለት ወር ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የስራ ውለን አቋርጧል። ስለዚህ መልስ ሰጭ /ተጠሪ/ ለአመልካች የሁለት ወር ደመወዝ ብር 10,697.96 /አስር ሺ ስድስት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከዘጠና ስድስት ሳንቲም/ ግብር ተቀንሶ የመክፈል ሃላፉነት አለበት። በላልች ነጥቦች የስር ፍ/ቤት የሰጠው ውሳኔ አልተነካም በማለት ውሳኔ ሰጥቷል።
አመልካች ጥር 17 ቀን 2007 ዓ/ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የስራ ውለ የተቋረጠው በህግ ከተደነገገው ውጭ መሆኑን ካረጋገጠ በኃላ የሁለት ወር ደመወዝ የማስጠንቀቂያ ክፍያ ብቻ እንዱከፈለኝ የሰጠው ውሳኔና የስር ፍርድ ቤት ለተጠሪ እንዱከፍል የተወሰነብኝን የጠበቃ አበል እና ኪሳራ ሳይሻር መቅረቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት አመልክቷል። ተጠሪ ግንቦት 13 ቀን 2007 ዓ/ም በሰጠው መልስ የአሰሪና ሰራተኛ ጉዲይ አዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 161 ሰራተኞቹን የዲኝነት ክፍያ ከመክፈል ነፃ የሚያደርግ እንጂ በአሰሪው ወጭና ኪሳራ እንዲይከፍለ የሚያደርግ ድንጋጌ አይደለም በማለት መልስ ሰጥቷል። አመልካች ግንቦት 25 ቀን 2007 ዓ/ም የተፃፈ የመልስ መልስ አቅርቧል።
ጉዲዩ በዚህ ሰበር ችልት የተያዘው ጭብጥ፤ የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ ይዘትና ግራ ቀኙ ያቀረቡት የጽሁፍ ክርክር ከላይ የተገለጸው ሲሆን እኛም ጉዲዩ ለዚህ ችልት ሲቀርብ የተያዘውን ጭብጥ ማለትም አመልካች ለተጠሪ ብር 6000 /ስድስት ሺ ብር/ የጠበቃ አበልና ኪሳራ እንዱከፍል የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ የህግ መሰረት አለው ወይስ የለውም? የሚለውን ጭብጥ ነጥብ መርምረናል።
ከላይ የተያዘውን ጭብጥ ለመወሰን ለያዝነው ጉዲይ አግባብነት ያላቸውን የፍታብሓር ስነ ስርዓት ህግ እና የአሰሪና ሰራተኛ ጉዲይ አዋጅ ቁጥር 377/96 ድንጋጌዎች መመርመር አስፈላጊ ነው። በፍርድ ቤት በሚደረግ ክርክር ተራቸው ስራቸው ኪሳራና ወጭ እንዱከፍል ፍርድ ቤቱ ሉያዝ እንደሚችልና ኪሳራ በቁጥር የተወሰነለት ወገን የተወሰነለትን የኪሳራ ገንዘብ፣ የወጭ ዝርዝር እንደሚያቀርብ የተፈቀደለት ደግሞ የወጭና ኪሳራ ዝርዝር አቅርቦ ለመጠየቅ የሚችል መሆኑን ከፍትሐብሕር ስነ-ስርዓት ህግ ቁጥር 463 ድንጋጌዎች ይዘት መረዲት ይቻላል። ይኸ የሥነ - ሥርዓት ህጉ ድንጋጌ አዋጅ 377/96 ቁጥር 161 ንዐስ አንቀጽ 2 “ማንኛውም ሰራተኛ ወይም የሰራተኛ ማህበር ፍርድ ቤት ለሚያቀርበው የስራ ክርክር ጉዲይ ከክፍያ” ነፃ ነው በማለት ካስቀመጠው ድንጋጌ ጋር ተጣጥሞ መታየት ያለበት ነው።
የአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 162 ንዐስ አንቀጽ 2 ድንጋጌ ከዲኝነት ክፍያ ነፃ ነው በሚል መንገድ ሳይሆን “ከክፍያ ነፃ ነው” በማለት የሚደነግግ መሆኑን ከድንጋጌው አቀራረጽና አውድ ንባብ ለማየት ይቻላል። ድንጋጌው የአሰሪና ሰራተኛ ጉዲይ አዋጅ ቁጥር 377/96 ህጋዊና ሰላማዊ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት የመፍጠር፤ የኢንደስትሪ ሰላምን የመፍጠር፤ በአሰሪና ሰራተኛ መካከል የሚነሳ ክርክር በተቀላጠፈ መንገድ መፍትሄ እንዱያገኝ የማድረግ አላማዎቹን በሚያሳካ ሁኔታ መተርጎምና ስራ ላይ መዋል ይኖርበታል። ከላይ የተገለጹትን አላማዎች ለማሳካት፤ ሰራተኞች በግልም ሆነ በጋራ መብታችን በአሰሪው ተጥሶብናል ብለው ሲያስቡ ጉዲዩን አይቶ ውሳኔ ለሚሰጥ ፍርድ ሰጭ አካል ከህግ አግባብና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዱታይላቸው ለመጠየቅ የሚችለበትን ተደራሽና ቀልጣፊ የዲኝነት ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል።
ከዚህ አንፃር ሲታይ ሰራተኛው በፍትሐብሄር ሥነ-ሥርዓት ህግ 465 ንኡስ አንቀጽ 1 በተደነገገው መሰረት ሰራተኛው ሀሰተኛና የተጨበረበረ ክስና ማስረጃ በአሰሪው ላይ ማቅረቡ ካልተረጋገጠ በስተቀር ከህግ አግባብ ውጭ ተጥሶብኛል የሚለውን የመብት ጥያቄ ለፍ/ቤት ወይም በህግ የዲኝነት ስልጣን ለተሰጠው አካል /አሰሪና ሰራተኛ ወሳኝ ቦርድ/ አቅርቦ በሙለ ወይም በከፉል ተረች በሆነ ጊዜ ሁለ አሰሪው ለክርክሩ ያወጣውን ወጭና ኪሳራ እንዱከፍል በሚያስገድድ መንገድ የአዋጅ አንቀጽ 161 ድንጋጌዎች ከተተረጎሙት ሰራተኞች ተጥሶብናል የሚለትን መብት ለማስከበር ክስ አቅርበን በፍርድ ቤት ተከራክረን ብንረታ አሰሪው ለጠበቃና ለክርክሩ የወጣውን ወጭ እንድንከፍል ሉወሰንብን ይችላል በሚል ፍራቻና ስጋት መብታቸውን በፍርድ ከመጠየቅ የሚገደቡበትን ሁኔታ የሚፈጥር ይሆናል። ይህም ከላይ የገለጽናቸውን የአዋጁን መሰረታዊ ዓላማዎች የሚያሳካ አይደለም። በመሆኑም ሰራተኛ ለአሰሪው በስራ ክርክር ምክንያት ያወጣውን ወጭና ኪሳራ የመክፈል ግዳታ የሚጣልበት በክርክሩ ተረች በመሆኑ ምክንያት ብቻ ሳይሆን ሰራተኛው በአሰሪው ላይ ያቀረበው ክስ ሀሰተኛና በተጭበርበረ ማስረጃ ላይ የተመሰረተ ሆኖ ሲገኝ መሆን እንዲለበት የፍታብሓር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 463 የፍትሐብሕር ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 465 ንዐስ አንቀጽ 1 ድንጋጌዎች ከአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 161 ድንጋጌ ጋር በሚጣጣም መንገድ በመተርጎም ለመረዲት ይቻላል።
በያዝነው ጉዲይ አመልካች ከህግ አግባብ የስራ ውለ ተቋርጦብኛል በሚል እምነት ክስ ያቀረበ መሆኑና በክርክር ሂደት አሰሪው /ተጠሪ/ያቀረበው ማስረጃ ከሰራተኛው /አመልካች/ የተሻለ ሆኖ ስለተገኘ የስር ፍርድ ቤት ስንብቱ ህጋዊ ነው በማለት የወሰነ መሆኑን ተረድተናል። ከዚህ በተጨማሪ አመልካችንና የተጠሪን ክርክር በይግባኝ ያየው የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ አመልካችን የስራ ውል ከማቋረጡ በፉት የሁለት ወር ማስጠንቀቂያ መስጠት ነበረበት በማለት ተጠሪ ለአመልካች የሁለት ወር ደመወዝ የማስጠንቀቂያ ክፍያ እንዱከፍል የወሰነ መሆኑን ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት ከሰጠው ውሳኔ ተረድተናል። ይህም አመልካች በክርክሩ ሙለ ለሙለ ተረች አለመሆኑንና በከፉል መብት ያለው መሆኑ ተረጋግጦ ውሳኔ የተሰጠለት መሆኑን ያሳያል።
ከላይ በዝርዝር ከሰጠነው የህግ ትርጉምና አመልካችና ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት እና በይግባኝ ካቀረቡት ክርክር መሰረታዊ ባህሪ አንፃር ሲታይ፣ አመልካች ለተጠሪ የጠበቃ አበል ብር 5000/ አምስት ሺ ብር/ ኪሳራ ብር 1000 /አንድ ሺ ብር/ በድምሩ ብር 6000 /ስድስት ሺ ብር/ እንዱከፍል የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው በማለት ወስነናል።
የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ታህሳስ 8 ቀን 2007 ዓ/ም የሰጠው ውሳኔ ተሻሽሎል።
የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ ለአመልካች የሁለት ወር ደመወዝ .96/ አስር ሺ ስድስት መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከዘጠና ስድስት ሳንቲም/ ግብር ተቀንሶ እንዱከፍል በማለት የሰጠው የውሳኔ ክፍል ጸንቷል።
የፋዳራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አመልካች በተጠሪ የጠበቃ አበል ብር 5000 /አምስት ሺህ ብር/ኪሳራ ብር 1000 /አንድ ሺ ብር/ በድምሩ ብር 6000 /ስድስት ሺብር/ እንዱከፍል የሰጠው የውሳኔ ክፍል ተሸሯል። አመልካች ይህንን ገንዘብ ለተጠሪ የመክፈል ኃላፉነት የለበትም በማለት ወስነናል።
በዚህ ፍርድ ቤት ያወጡትን ወጭና ኪሳራ ግራ ቀኙ በየራሳቸው ይቻለ ።
መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ።
No topics extracted.