የአንድ ድርጅት ሰራተኛ ለአሰሪው የስራ መልቀቂያ አስገብቶ የስራ መልቀቂያው በአሰሪው ምክንያት በወቅቱ ሣይሰጠው ቆይቶ ሰራተኛው የስራ ግዳታውን እየተወጣና የስራ ግንኙነታቸው በተግባር ቀጥል ባለበት ሁኔታ ከረጅም ጊዜ በኋላ አሰሪው ሰራተኛው ቀደም ብል ያስገባውን የስራ መልቀቂያ መሰረት በማድረግ የስራ ውለን ቢያቋርጥ የስራ ውለ የተቋረጠው በህገወጥ መንገድ ነው ልባል የሚችል ስለመሆኑ፣ አዋጁ ቁ.377/96 አንቀፅ 4/1/፣23፣26፣30፣31፣33፣39፣40/2/፣43/4/ሀ/፣ 35/1/ለ/፣38
No summary available.
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ዳኞች-፡- አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፊ አህመድ ተኽሉት ይመሰል አመልካች፡- ሴንቸሪ ጄኔራል ትሬዱንግ ኃላፉነቱ የተወሰነ የግል ማህበር - ጠበቃ አሰፊ ዓሉ ቀረቡ ተጠሪ፡- አቶ ገስጥ ንጉሴ - ቀረቡ መዝገቡ ተመርምሮ የሚከተለው ፍርድ ተሰጥቶአል።
ጉዲዩ የአሰሪና ሰራተኛ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን የተጀመረውም በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሳሽ የነበሩት የአሁኑ ተጠሪ በአሁኑ አመልካች ላይ በ11/09/2006 ዓ.ም አዘጋጅተው ባቀረቡት ክስ ነው። የክሳቸውም ይዘት ባጭሩ፡-ከሳሽ ከ09/03/2006 ዓ.ም ጀምሮ በአሽከርካሪነት የስራ መደብ ላይ በወር ያልተጣራ ብር 1,900 (አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ) ደመወዝ እየተከፈላቸው በተከሳሽ ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ እያለ ተከሳሽ ድርጅት ካለአንዲች ምክንያት በ19/07/2006 ዓ.ም ከስራ ካገዲቸው በኃላ በ24/08/2006 ዓ.ም በተጻፈ ደብዲቤ ከስራ ያሰናበታቸው መሆኑን የሚገልጽ ሆኖ የስራ ስንብት እርምጃው ሕገወጥ ነው ተብል ሕገ ወጥ የስራ ስንብት የሚያስከትላቸውን እና ተዛማጅ ክፍያዎችን በድምሩ ብር 21,850 (ሃያ አንድ ሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ) ድርጅቱ እንዱከፍላቸው ይወሰን ዘንድ ዲኝነት የተጠየቀበት ነው።
ተከሳሽ ድርጅት በበኩለ በ26/09/2006 ዓ.ም. በሰጠው መልስ የከሳሽ የስራ ውል እንዱቋረጥ የተደረገው ከሳሽ ስራቸውን ለመስራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው፣አሮጌ ተሽከርካሪ አላሽከረክርም በማለታቸው፣ከድርጅቱ ሰራተኞች ጋር ለመስራት ባለመቻላቸው፣በዚህም ምክንያት የድርጅቱ ሰራተኞች በከሳሽ ሾፋርነት በድርጅቱ ተሽከርካሪ ከመጠቀም ይልቅ በታክሲ መጠቀም ይሻለናል በማለታቸው እና ከሳሽ ተደጋጋሚ ምክር እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ሉታረሙ ባለመቻላቸው በመሆኑ የስራ ውላቸው የተቋረጠው በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 13(2) መሰረት በአግባቡ ነው፣እስከሰሩበት መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ያለው ደመወዝ ተከፍሎቸዋል ፣ያልሰሩበት የሚያዝያ ወር ደመወዝ እንዱከፈላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፣የዘገየ ክፍያ የለም፣ በመሆኑም ክሱ ውድቅ ላደረግልን ይገባል በማለት ተከራክሯል።
ፍርድ ቤቱም ክሱን እና የግራ ቀኙን ምስክሮች ከሰማ በኃላ አጠቃላይ ክርክሩን መርምሮ ከሳሽ ባላቸው የማሽከርከር ሙያ በተቀጠሩበት የስራ መደብ ሰራተኞችን ወደ ስራ ቦታ በሰዓቱ ወስደው በሰዓቱ መመለስ እና የሚሰጣቸውን ትዕዛዝም መፈጸም እንዲልቻለ እንዱሁም ተሽከርካሪው መስራት የሚችል ሆኖ እያለ በአሮጌ ተሽከርካሪ አልሰራም በማለት አቁመው እንደሄደ ከግራ ቀኙ ምስክሮች ቃል መገንዘብ መቻለን፣አንድ ሰራተኛ በአሰሪው የሚሰጠውን ትዕዛዝ የመፈጸም ግዳታ ያለበት ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 13 (2) ስር ተደንግጎ የሚገኝ መሆኑን፣ይሁን እንጂ ከሳሽ መፈጸማቸው የተረጋገጠው ጥፊቶች በአዋጁ አንቀጽ 27 መሰረት ካለማስጠንቀቂያ ከስራ የሚያሰናብቱ አለመሆኑን ገልጾ ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት ተከሳሽ ድርጅት ሕገ ወጥ የስራ ስንብት የሚያስከትላቸውን ክፍያዎች ለከሳሽ እንዱከፍል እና የስራ ልምድ ማስረጃ እንዱሰጣቸው ውሳኔ ሰጥቷል።አመልካች አቤቱታውን ለዚህ ችልት ያቀረበው የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኙን ዘግቶ በማሰናበቱ የስር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሉታረም ይገባል በማለት ሲሆን የሰበር አቤቱታው ተመርምሮ በዚህ ጉዲይ ተጠሪው በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 13 የተመለከተውን ግዳታ ሉፈጽም ያልቻለ መሆኑ በፍሬ ነገር ደረጃ የተረጋገጠ ቢሆንም የዚህ ግዳታ መጓደል ካለማስጠንቀቂያ የስራ ውል ለማቋረጥ የሚያስችል ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ 27(1) ስር ስላልተካተተ ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት በስር ፍርድ ቤቶች የተሰጠውን ትርጉም አግባብነት ተጠሪው ባለበት ለማጣራት ይቻል ዘንድ ጉዲዩ ለሰበር ክርክር እንዱቀርብ በመደረጉ ግራ ቀኙ የጽሁፍ ክርክር ተለዋውጠዋል።
የጉዲዩ አመጣጥ እና የክርክሩ ይዘት ከላይ የተመለከተው ሲሆን እኛም አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት መሆን አለመሆኑን ለክርክሩ ከተያዘው ጭብጥ አንጻር መርምረናል።
በዚህም መሰረት ጉዲዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት በአንድ በኩል ተጠሪው ባላቸው የማሽከርከር ሙያ በተቀጠሩበት የስራ መደብ ሰራተኞችን ወደ ስራ ቦታ በሰዓቱ ወስደው በሰዓቱ መመለስ እና የሚሰጣቸውን ትዕዛዝም መፈጸም እንዲልቻለ እንዱሁም ተሽከርካሪው መስራት የሚችል ሆኖ እያለ በአሮጌ ተሽከርካሪ አልሰራም በማለት አቁመው እንደሄደ በግራ ቀኙ ምስክሮች መረጋገጡን እና አንድ ሰራተኛ በአሰሪው የሚሰጠውን ትዕዛዝ የመፈጸም ግዳታ ያለበት ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 13 (2) ስር ተደንግጎ የሚገኝ መሆኑን በውሳኔው ላይ ከገለጸ በኃላ በልላ በኩል ግን ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት ለተጠሪው የተለያዩ ክፍያዎች እንዱከፈለ ውሳኔ የሰጠው ተጠሪው መፈጸማቸው የተረጋገጠው ጥፊቶች በአዋጁ አንቀጽ 27 መሰረት ካለማስጠንቀቂያ ከስራ የሚያሰናብቱ አይደለም በማለት ነው።በመሰረቱ የስራ ውል ማለት ማንኛውም ሰው ደመወዝ እየተከፈለው በአሰሪ መሪነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ወይም የተወሰነ ስራ ለአሰሪው ለመስራት ግዳታ የሚገባበት ውል ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 በአንቀጽ 4 (1) ስር የተመለከተ ሲሆን የዚህ ዓይነት የውል ግዳታ የገባ ሰራተኛ በስራ ውለ ላይ የተመለከተውን ስራ ራሱ የመስራት፣በስራ ውለ እና በስራ ደንቡ መሰረት በአሰሪው የሚሰጠውን ትዕዛዝ መፈጸም እና የአዋጁን ድንጋጌዎች፣የሕብረት ስምምነትን፣የስራ ደንብን እና በሕግ መሰረት የሚተላለፈ መመሪያዎችን እና ትዕዛዞችን የማክበር ግዳታ ያለበት ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ 13 (1) (2) እና (7) ድንጋጌዎች ስር ተመልክቷል። በተጠሪው መፈጸማቸው በግራ ቀኙ ምስክሮች እንደተረጋገጡ በስር ፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የተገለጹት ፍሬ ነገሮችም ተጠሪው ከላይ በተጠቀሱት የአዋጁ ድንጋጌዎች የተመለከቱትን ግዳታዎች መፈጸም አለመቻላቸውን በግልጽ የሚያስገነዝቡ ናቸው።ተጠሪው እነዚህን ግዳታዎች ለመፈጸም ፈቃደኛ አለመሆናቸው ደግሞ ከአመልካች ጋር የገቡትን የስራ ውል መሰረታዊ ዓላማ እና ይዘት የሚጻረር እና የስራ ውለን ተግባራዊነት የሚያሰናክል ከመሆኑም በላይ ድርጊቶቹም በባህሪያቸው ሆን ተብለው የሚፈጸሙ በመሆኑ እንደተራ ጥፊት ተቆጥረው በቀላለ ሉታለፈ የሚገባቸው አይደለም። በተጠሪው መፈጸማቸው የተረጋገጡት ጥፊቶች ካለማስጠንቀቂያ ከስራ የሚያሰናብቱ ናቸው ተብለው በአዋጁ አንቀጽ 27 (1) ስር ከተዘረዘሩት ጥፊቶች ውስጥ በግልጽ ባይጠቀሱም በአሰሪው ንብረት ወይም ከድርጅቱ ስራ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ባለው በማናቸውም ንብረት ላይ ሆነ ብል ወይም በከባድ ቸልተኝነት ጉዲት ማድረስ ካለማስጠንቀቂያ ከስራ ሉያሰናበት የሚችል ጥፊት ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ 27 (1) (ሸ) ስር ተመልክቷል።በመሰረቱ …”የአሰሪው ንብረት…” በሚል በዚህ ድንጋጌ ስር የተቀመጠው አገላለጽ መተርጎም የሚገባው ግዙፍነት ያለው ቁሳዊ አካል ብቻ ተደርጎ ሳይሆን ለአሰሪው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የሚያስገኝ ማናቸውንም ላላ ነገር በሚያካትት አግባብ ነው።በተያዘው ጉዲይ በተጠሪው መፈጸማቸው የተረጋገጡት ጥፊቶች የአሰሪውን የስራ እንቅስቃሴ የማስተጓጎል ውጤት ያስከተለ መሆናቸው ተረጋግጧል።ይህ መሆኑ ደግሞ ተጠሪው ሆነ ብለው በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዲት ማድረሳቸውን መገንዘብ የሚያስችል ነው።በመሆኑም ጉዲዩን በመጀመሪያ ደረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤት ተጠሪው በአዋጁ አንቀጽ 13 (1) (2) እና (7) ድንጋጌዎች ስር የተመለከቱትን ግዳታዎች አለመወጣታቸው የሚያስከትለውን ሕጋዊ ውጤት በአዋጁ አንቀጽ 27 (1) (ሸ) ስር ከተመለከተው ድንጋጌ አንጻር አይቶ መተርጎም ሲገባው ተጠሪው በአዋጁ አንቀጽ 13(2) ስር የተመለከቱትን ግዳታዎች አለመፈጸማቸው ካለማስጠንቀቂያ የስራ ውል ለማቋረጥ የሚያስችለ ናቸው ተብለው በአዋጁ አንቀጽ 27 (1) ስር ከተዘረዘሩት ጥፊቶች ስር በግልጽ አልተጠቀሱም ከሚል ድምዲሜ ላይ በመድረስ ስንብቱ ሕገወጥ ነው በማለት የሰጠው እና በከፍተኛ ፍርድ ቤት ተቀባይነት ያገኘው ውሳኔ ሕጋዊ መሰረት ያለው ነው ለማለት የሚቻል ሆኖ አልተገኘም።
ሲጠቃለል ስንብቱ ሕገ ወጥ ነው በማለት ሕገ ወጥ የስራ ስንብት እርምጃ የሚያስከትላቸውን ክፍያዎች አመልካች ለተጠሪው እንዱከፍል በስር ፍርድ ቤቶች የተሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ የሚከተለው ውሳኔ ተሰጥቷል።
ስንብቱ ሕገ ወጥ ነው በማለት ሕገ ወጥ የስራ ስንብት እርምጃ የሚያስከትላቸውን ክፍያዎች አመልካች ለተጠሪው እንዱከፍል በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ በ29/11/2006 ዓ.ም ተሰጥቶ በፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ በ20/04/2007 ዓ.ም. በትዕዛዝ የጸናው ውሳኔ በፍትሐብሕር ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 348(1) መሰረት ተሽሮአል።
በአመልካች የተወሰደው የስራ ስንብት እርምጃ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 13 (1) (2) እና (7) እና 27 (1) (ሸ) መሰረት ሕጋዊ ነው በማለት ወስነናል።
የተጠሪውን የስራ መደብ፣የደመወዝ መጠን እና የአገልግልት ዘመን በመጥቀስ አመልካች የስራ የምስክር ወረቀት እንዱሰጣቸው በስር ፍርድ ቤቶች የተሰጠው የውሳኔ ክፍል አልተነካም።
እንዱያውቁት የውሳኔው ግልባጭ ለስር ፍርድ ቤቶች ይላክ።
የሰበር ክርክሩ ያስከተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻለ።
ውሳኔ ያገኘ ስለሆነ መዝገቡ ተዘግቷል።