No summary available.
መጋቢት 4 ቀን 2007 ዓ/ም ዳኞች፡- አልማው ወል ዓላ መሐመድ ሡልጣን አባተማም ሙስጠፋ አህመድ ተኽላት ይመሰል አመልካች፡- አቶ ዕቁባይ በርሀ ገ/እግዚአብሕር - ጠበቃ ደሳለኝ መስፍን ቀረቡ ተጠሪ፡- የኢትዮጵያ ገቢዎች ጉምሩክ ባለሥልጣን - ዐ/ህግ ወንድዬ ብርሃኑ ቀረቡ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል
ጉዳዩ የቀረበው አመልካች የፍድራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ታህሳስ 19/2005 ዓ/ም የሰጠው ፍርድና የፍድራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመዝገብ ጥር 21 ቀን 2006 ዓ/ም የሰጠው ፍርድ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታርምልኝ በማለት ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው ጉዳዩ ተጠሪ አመልካች የአንድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ሲሰራ ለግብር ስብሳቢው መሥሪያ ቤት አሳሳች ማስረጃ የማቅረብና ተጨማሪ እሴት ታክስ የማሳወቅና የመክፈል ኃላፊነቱን ባለመወጠት ወንጀል ፈፅሟል በማለት ያቀረበውን ክስና ክርክር የሚመለከት ነው። በሥር ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል።
አንደኛ ተከሳሽ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 286 /1994 አንቀፅ 97 ንዑስ አንቀፅ 3(ሀ) የተመለከተውን በመተላለፍ 1997 ዓ/ም ባከናወነው የንግድ እንቅስቃሴ ትርፍ አግኝቶ እያለ፤ ወጭውን ከፍ አድርጎ በማቅረብ ኪሣራ እንደደረሰበት አድርጎ በማሳወቁ፤ ለግብር ሰብሳቢው መሥሪያ ቤት አሳሳች ማስረጃ የማቅረብ ወንጀል ፈፅሟል ሁለተኛው ተከሳሽ (አመልካች) የአንደኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ ሆኖ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀፅ 96 ንዑስ አንቀጽ 3(ሀ) አንቀፅ 102(1) የተመለከተውን በመተላለፍ አሳሳች ማስረጃ የማቅረብ ወንጀል ፈፅሟል።
አንደኛ ተከሳሽ በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 285 /94 አንቀፅ 49 እና በወንጀል ህግ አንቀፅ 34(ሀ) የተመለከተውን በመተለለፍ ከ1996 ዓ/ም እስከ 2002 ዓ.ም ባደረገው የንግድ እንቅስቃሴ የሰበሰበውን ብር 426.229.03 /አራት መቶ ሃያ ስድስት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ ዘጠኝ ብር ከዜሮ ሶስት ሣንቲም) ተጨማሪ እሴት ታክስ ለመንግስት አሳውቆ ባለመክፈሉ ወንጀል ፈፅሟል።ሁለተኛ ተከሳሽ (አመልካች) የአንደኛ ተከሳሽ ሥራ-አስኪያጅ ሆኖ ሲሰራ አንደኛ ተከሳሽ የሰብሰበውን ተጨማሪ እሴት ታክስ ለመንግስት አሳውቆ እንዲከፈል ባለማድረጉ በአዋጅ ቁጥር 285/1994 ዓንቀፅ 49 እና 56(1) በመተላለፍ ወንጀል ፈፅሟል በማለት ክስ አቅርቧል።
2 አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ቀርቦ ወንጀሉን አልፈፀምኩም ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት የቀረበበትን ክስ ክዶ ተከራክሯል። ተጠሪ የአንደኛ ተከሳሽ የንግድ ፈቃድ፤ ሜጋ ኪነጥበብ ማዕከል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የመመሥረቻ ፅሑፍና መተዳደሪያ ደንብ የድርጅቱ ገቢ ኦዲት የተሰራበት ሪፖርትና የትርፍ ማስታወቂያ፣ ደረሰኝ የተተመበትን ሰነድና የሰው ምስክሮችን በማስረጃነት አቅርቧል። ተጠሪ ያቀረባቸው ሁለት ምስክሮች አንደኛ ተከሳሽ የመፍረስ ጥያቄ በማቅረቡ ከሳሽ መሥሪያ ቤት የድርጅቱን ሒሳብ ኦዲት እንዲያደርጉ መድቧቸው ሒሳቡን ኦዲት ያደረጉ መሆኑን ሂሳቡን ኦዲት ያደረጉት የአንደኛ ተከሳሽ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት ሁለተኛ ተከሳሽ ያቀረበውን የሂሳብ ሰነድና አንደኛ ተከሳሽ ለከሳሽ መሥሪያ ቤት ሲያቀርብ የነበረውን የሂሳብ ሪፖርት መሰረት በማድረግ እንደሆነ ገልፀው 1997 ዓ/ም አንደኛ ተከሳሽ ብር 15,748 /አስራ አምስት ሺህ ሰባት መቶ አርባ ስምንት ብር/ ኪሳራ የደረሰበት መሆኑን ለከሳሽ አሳውቋል። ሆኖም 1997 ዓ/ም አንደኛ ተከሳሽ ብር 132,673.06/አንድ መቶ ስላሣ ሁለት ሺ ስድስት መቶ ሰባ ሶስት ብር ከዜሮ ስድስት ሣንቲም/ አግኝቶ የነበረ መሆኑንና 1997 ዓ/ም አንደኛ ተከሳሽ 39.801 /ስላሳ ዘጠኝ ሺህ ስምንት መቶ አንድ ብር) የንግድ ትርፍ ገቢ ግብር መክፈል የነበረበት መሆኑን በማረጋገጥ ወስነናል። አንደኛ ተከሳሽ ኪሣራ ደርሶብኛል በማለት ሪፖርት ያደረገው የድርጅቱ ሰራተኞች ባልሆኑ ሰዎች የከፈለው ደመወዝ የስልክ ወጭና የልላ ድርጅት ንብረት የሆኑ መኪኖች የተሞላ ነዳጅ በወጭነት በማቅረብ ነው። ይህም የገቢ ግብር አዋጅንና አዋጁን ለማስፈፀም የወጣውን መመሪያ መሰረት ያላደረገ በመሆኑ በወጭነት አልያዝነውም። እኛ ሂሳብ ስንሰራ ወድቅ አድርገነዋል።
3 ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪ ተጨማሪ እሴት ታክስን በተመለከተ አንደኛ ተከሳሽ ለከሳሽ ባሣወቀውና አንደኛ ተከሳሽ ባከናወነው ግብይት ወይም የንግድ እንቅስቃሴ መካከል ልዩነት መኖሩን አንደኛ ተከሳሽ ብር 429,172 /አራት መቶ ሃያ ዘጠኝ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ሁለት ብር/ ተጨማሪ እሴት ታክስ ለመንግስት አሳውቆ መክፈል ሲገባው፤ ይህንን የተጨማሪ እሴት ታክስ ለመንግስት ያልከፈለ መሆኑን ባከናወኑት የኦዲት ሥራ ማረጋገጣቸውን ለሥር ፍርድ ቤት ያስረዱ መሆኑን በውሣኔው አስፍሮታል። ሶስተኛው የተጠሪ ምስክር አንደኛ ተከሳሽ የሂሳብ ሰራተኛ መሆኑን ገልፆ ሁለተኛው ተከሳሽ የአንደኛ ተከሳሽ ሥራ አስኪያጂ በመሆን 1997 ዓ/ም እስከ 2002 ዓ/ም የሰራ መሆኑንና 1ኛ ተከሳሽ 1998 ዓ/ም ከሜጋ ማስታወቂያ ጋር ሲዋሀድም 2ኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ ሆኖ የሰራ መሆኑን እንደመሰከረ የሥር ፍርድ ቤት በውሳኔው ፅፎታል።
4 ሁለተኛ ተከሳሽ /አመልካች/ ተጨማሪ እሴት ታክስ የሂሳብ ሰራተኞች በየወሩ ለከሳሽ /ተጠሪ/ ሪፖርት ያደርጉ የነበረ መሆኑንና ገቢን አለማሳወቅና አሳሳች ማስረጃ ማቅረብ የተባለውም ገቢን አለማሣወቅና አሳሳች ማስረጃ የማቅረብ ወንጀል አልፈፀምኩም በኦዲት ተገኘ የተባለው የሂሳብ ልዩነት የተፈጠረው አንደኛ ተከሳሽና ሜጋ ማስታወቂያ 1998 ዓ/ም ጀምሮ በአንድ ሥራአስኪያጅ እየተመሩ አንድ ላይ ስራ ሲሳሩ የነበረ በመሆኑና በሜጋ ማስታወቂያ ሰረተኞች የስልክ ወጭና የሜጋ ማስታወቂያ መኪኖች ነዳጅ የወጣ ውጭ በመኖሩ ምክንያት ነው በማለት አምስት የመከላከያ ምስክሮችን አቅርቦ አሰምቷል።
አንደኛው የአመልካች የመከላከያ ምስክር የአንደኛ ተከሳሽ ጉዳይ አስፈፃሚ ሆኖ ሲሳራ ከፋይናንስ ክፍል ይሰጠው የነበረውን የተጨማሪ እሴት ተክስ ሪፖርት ለከሳሽ /ለተጠሪ/ ሲያደርስ እንደነበረና አንደኛ ተከሳሽ 1998 ጀምሮ ከሜጋ ማስታወቂያ ጋር ሲሰራ የሜጋ ማስታወቂያና መኪኖች በትውስት በመውሰድ ነዳጅ በመሙለት ሲጠቀም እንደነበረ የመሰከረ መሆኑን ሁለተኛ መከላከያ ምስክር የሒሳብ ባለሙያ መሆናቸውን ገልፀው ለአንደኛ ተከሳሽ የሂሳብ ሰራተኞች በ1996 ዓ/ም የሂሳብ አያያዝ ሥልጠና የሰጡ መሆኑን እንደመሰከረ፣ ሶስተኛ መከላከያ ምስክር የአንደኛ ተከሳሽ የሂሳብ ሰራተኛ እንደነበር 1997 ዓ/ም ጀምሮ የሽያጭ ወጭ ደረሰኞችን በመቀበል በየወሩ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሪፖርት ያዘጋጅ እንደነበር እንደመሰከሩ፤ አራተኛ የመከላከያ ምስክር የአንደኛ ተከሳሽ ሹፍር የነበረ መሆኑን ገልጾ፣ 1ኛ ተከሳሽ ይጠቀምበት የነበረውን ላንድክሩዘር ኮድ ሁለት የሆነ መኪና ያሽከረክር እንደነበርና ወጭውንም የሚሸፍነው አንደኛ ተከሳሽ እንደነበር እንደመሰከረ፣ 5ኛ የመከላከያ ምስክር የፋሲል ኮንሰልት ኃላ/የተ/የግል ማህበር የሂሳብ ሰራተኛ በመሆን የአንደኛ ተከሳሽ የሁለት አመት 1996ዓ.ም እና 1997ዓ.ም ሂሳብ የሰራ መሆኑንና የሂሳብ ሰነድ ወጭና ገቢ አያያዙ ጥሩ ሆኖ ማግኘታቸውንና ተከሳሽ ድርጅትም በኪሳራ ይንቀሳቀስ እንደነበር ያስረዱ መሆኑን የስር ፍርድ ቤት በውሳኔው አስፍሮታል።
5 የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽና ሜጋ ማስታወቂያ አግባብነት ባለው ሕግ መሰረት ያልተቀላቀለ መሆኑ፣ አንደኛ ተከሳሽ በሜጋ ማስታወቂያ ሰራተኞች የከፈለው ደመወዝና የስልክ ወጭ የአንደኛ ተከሳሽ ሕጋዊ ወጭ ተደርጎ ላያዝ የማይችል መሆኑን የተሽከርካሪ ትውስት የተባለውም ተቀባይነት ያለውን የሂሳብ አሰራር ያልተከተለ በመሆኑ ተጨማሪ እሴት ታክስን በተመለከተ፣ በየወሩ ሪፖርት ይደረግ የነበረ መሆኑን በመከላከያ ማስረጃ ከማስረዳት ውጭ አንደኛ ተከሳሽ የሰበሰበውን ብር 426,229.03 ተጨማሪ እሴት ታክስ ለከሳሽ መስሪያ ቤት ያላሳወቀና ገቢ ያላደረገ መሆኑን በማረጋገጥ በከሳሽ (ተጠሪ) በኩል ያቀረበውን ማስረጃ የሚያስተባብል ማስረጃ አልቀረበም። ስለዚህ አንደኛ ተከሳሽ 1997ዓ.ም ትክክለኛ ገቢውን ባለማሳወቁና ኪሳራ እንደደረሰበት ሪፖርት በማድረጉ እንደዚሁም አንደኛ ተከሳሽ ከ1996ዓ.ም እስከ 2002ዓ.ም የሰበሰበውን ተጨማሪ እሴት ታክስ ሙሉ ለሙሉ ለተጠሪ (ለከሳሽ) ባለማሳቁና ገንዘቡንም ገቢ ባለማድረጉ ሁለተኛ ተከሳሽ በስራ አስኪያጅነቱ በአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 96 እና አንቀጽ 97 ንዑስ አንቀጽ 3(ሀ) የተመለከተውን በመተላለፍና በአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 49 የተመለከተውን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመ ጥፋተኛ ነው በማለት የቅጣት ውሳኔ በመወሰንና በመገደብ ውሳኔ ሰጥቷል።
6 በዚህ ውሳኔ አመልካችና ተጠሪ ቅር በመሰኘት አመልካች በመዝገብ ተጠሪ በመዝገብ ያቀረቡትን ይግባኝ ቅሬታ በፍድራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ በማጣመር፣ የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን የጥፋተኝነት ውሳኔ በማጽናት ውሳኔ ሰጥቷል።
7 አመልካች የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡትን የጥፋተኝነት ውሳኔ ለማስለወጥ ሚያዚያ 17 ቀን 2006 ዓ.ም በተጻፈ የሰበር አቤቱታ ተጠሪ የወንጀል ክስ ከመመስረቱ በፊት የንግድ ድርጅት ስራ አስኪያጅነት መልቀቄን ሰነዶች ያረጋግጣሉ። እኔ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ በወንጀል ጥፋተኛ ልባል ከሚገባው በመጀመሪያ በስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ የነበረው የንግድ ድርጅት ተጠርቶ፣ ቀርቦ ተከራክሮ በወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ ሲገኝ ነው። አንደኛ ተከሳሽ የልለ መሆኑን ተጠሪ የወንጀል ክስ ሲመሰርት ያውቃል። አንደኛ ተከሳሽ የፈረሰና ህጋዊ ህልውና የልለው በመሆኑ በወንጀል ላከሰስና ጥፋተኛ ተብሎ ላቀጣ አይችልም።
አንደኛ ተከሳሽ በወንጀል ላጠየቅ የማይችል ከሆነ ስራ አስኪያጅ በወንጀል ላጠየቅ አይችልም ። የአንደኛ ተከሳሽ ሂሳብ ኦዲት የተደረገው በ2003 ዓ.ም ነው። ይህም አመልካች ድርጅቱን ከለቀቀ ከአስር ወር በኋላ ነው። ሜጋ ማስታወቂያና ሜጋ ኪነጥበባት፣ በኋላ የተቀላቀሉ መሆኑ ተረጋግጧል። ስለዚህ ስራ አስኪያጅ የነበረው አመልካች በተጨባጭ ለስራ ያወጣው ወጭ ውድቅ ተደርጎ አሳሳች ማስረጃ አቅርቧል፣ ተጨማሪ እሴት አሳውቆ ገቢ አላደረገም ተብሎ የተሰጠው የጥፋተኝነት ውሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልኝ በማለት አመልክቷል።
8 ሰኔ 27 ቀን 2006ዓ.ም በተጻፈ መልስ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ድርጅት በራሱ ወንጀል የመፈጸም ሃሳብ የሚፈጥር ባለመሆኑ፣ ድርጅቱ ወንጀል የሚፈጽመው ከድርጅቱ ኃላፊዎች ወይም ሰራተኞች አንዱ የድርጅቱን ህጋዊ ግድታ ባለመወጣት ወይም የድርጅቱን ጥቅም በህገ ወጥ መንገድ ለማራመድ ተንቀሳቅሰው በተገኙ ጊዜ ነው። ከስር ሁለተኛ ተከሳሽ የነበሩት አመልካች አንደኛ ተከሳሽ የነበረው ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ በነበሩበት ጊዜ ለተፈጸመው ወንጀል ተጠያቂ መሆናቸው በወንጀል ሕጉ የተቀመጠውን መርህ የተከተለ ነው። ከስር አንደኛ ተከሳሽ የነበረው ድርጅት በህጋዊ መንገድ የፈረሰ ስለመሆኑ የቀረበ ማስረጃ የለም። ተጠሪ የወንጀል ክሱንና መጥሪያውን ለማድረስ ጥረት አድርጎ ላያገኘው አልቻለም። ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በጋዜጣ ጥሪ አድርጎለት አልቀረበም ከዚህ አንጻር የስር ፍርድ ቤት በጋዜጣ አለመጥራት እንደ ስነስርዐት ስህተት ከሚታይ በስተቀር በአመልካች ላይ የተሰጠውን ውሳኔ የሚያስለውጥ አይደለም። የድርጅቱም ሂሳብ በአግባቡ የተጣራና ወንጀሉ የተፈጸመ መሆኑ ተረጋግጦ የተሰጠ ውሳኔ በመሆኑ የአመልካች፣ የሰበር አቤቱታ ውድቅ ይደረግልኝ በማለት መልስ ሰጥቷል። አመልካች ነሐሴ 23 ቀን 2006 ዓ.ም በተጻፈ የመልስ መልስ ሁለተኛ ተከሳሽ (አመልካች) በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ የሚረጋገጠው አንደኛው ተከሳሽ በአግባቡ ተጠርቶ፣ ተከራክሮ ጥፋተኛ ነህ ተብሎ ሲፈረድበት ነው። ይህ ሳይደረግ ሁለተኛው ተከሳሽ ጥፋተኛ ተብሎ ላፈረድበት አይችልም። የስር ፍርድ ቤት ድርጅቱንና ሁለተኛ ተከሳሽን ጥፋተኛ ናቸው በማለት ውሳኔ ሰጥቷል። ይህ ተገቢ ያልሆነና የወንጀል ህግን መሰረታዊ መርህ የሚጻረር ውሳኔ ነው። ምክንያቱም በስር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ ተከሳሽን በመጥሪያም ይሁን በጋዜጣ አልተጠራም፣ አልቀረበም በልለበት ይታያል ተብሎ አልተያዘም። 1ኛ ተከሳሽ ያፈረሰ መሆኑን የማስረዳት ግድታ ሁለተኛ ተከሳሽ የለብኝም የሚልና ልሎች በሰበር አቤቱታው ያነሳቸውን መከራከሪያዎች የሚያጠናክር ክርክር አቅርቧል።
9 ከስር የክርክሩ አመጣጥና ግራ ቀኙ በዚህ ሰበር ችሎት ያቀረበው የጽሑፍ ክርክር ከላይ የተገለጸው ሲሆን እኛም የበታች ፍርድ ቤቶች አመልካች የሜጋ ኪነጥበባት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር ስራ አስኪያጅ ሆኖ ሲሰራ፣ የንግድ ትርፍ ገቢ በትክክል አለማሳወቅና የንግድ ትርፍ ገቢ ግብር አለመክፈል፣ አሳሳች ማስረጃ የማቅረብና የንግድ ድርጅቱ በፈጸማቸው ግብይቶች ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሰበሰበውን ተጨማሪ እሴት ታክስ በተሟላ ሁኔታ አለማሳወቅና ገቢ ያለማድረግ ወንጀል ፈጽሟል በማለት የሰጡት የጥፋተኝነት ውሳኔ በሕግ አግባብ የተሰጠ ነው ወይስ አይደለም? የሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምረናል።
10 ጉዳዩን እንደመረመርነው የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ የሆነው ሜጋ ኪነጥበባት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር በንግድ ህግ አንቀጽ 542 እና አንቀጽ 543 መሰረት ያልፈረሰ ወይም የንግድ ህጉ ከአንቀጽ 544 እስከ አንቀጽ 554 በተደነገጉት ድንጋጌዎች መሰረት ከልላ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር በተለይም ከሜጋ ማስታወቂያ ጋር በሕግ የተደነገገውን ስርዓት በማሟላት ያልተቀላቀለ መሆኑ የስር ፍርድ ቤት በውሳኔው በማረጋገጥ ውሳኔ ሰጥቷል የስር አንደኛ ተከሳሽ በህግ አግባብ ካልፈረሰ ወይም ከልላ የንግድ ድርጅት ጋር አለመቀላቀሉ ካልተረጋገጠ፣ ህጋዊ ህልውና ያለው ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ እንደሆነ ከህጉ ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል። የስር አንደኛ ተከሳሽ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በመሆኑ ከመፍረሱ ወይም ከልላ ድርጅት ጋር ከመቀላቀሉ በፊት ይከናወን ያላቸው ተግባራት አሉ። ከእነዚህ ተግባራት መካከል የማኃበሩ ሒሳብ የማጣራት ስራ ነው። ተጠሪ የአንደኛ ተከሳሽ ሂሳብ ኦዲት ያደረገው አንደኛ ተከሳሽ የመፍረስ ጥያቄ በማቅረቡ እንደሆነ፣ ተጠሪ ያቀረባቸው ምስክሮችና የአንደኛ ተከሳሽን ሒሳብ ያጣሩት ባለሙያዎች የገለጹ መሆኑን በስር ፍርድ ቤት በግልጽ ሰፍሯል። ይህም የአንደኛ ተከሳሽ ሒሳብ በተጣራበት ጊዜ አንደኛ ተከሳሽ የመፍረስ ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም በሕግ አግባብ ሒሳቡ ተጣርቶ የመፍረስ ውሳኔ ያልተሰጠና ህጋዊ ሕልውና ያለው ድርጅት የነበረ መሆኑን የበታች ፍርድ ቤቶች ፍሬ ጉዳይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ስልጣናቸው ያረጋገጡት በመሆኑ አመልካች አንደኛ ተከሳሽ ሕጋዊ ሕልውናው የከተመ ወይም የፈረሰ ድርጅት ነው በማለት ያቀረበው ክርክር የሕግ መሰረት ያለው ሆኖ አላገኘነውም።
11 .አንደኛ ተከሳሽ የሕግ ሰውነት ያለው የንግድ ድርጅት ነው። የሕግ ሰውነት ያለው የንግድ ድርጅት በሕግ በግልጽ በተደነገገ ጊዜ በዋና ወንጀል አድራጊነት፣ በአነሳሽነት ወይም በአባሪነት ወንጀል ላቀጣ የሚችል መሆኑ ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶች ሕጉ በወንጀል የሚጠየቁ እንደሆነ በልዩ ሁኔታና በግልጽ ባልደነገገባቸው ወንጀሎች የወንጀል ተጠያቂነት እንደማይኖርባቸው በወንጀል ህጉ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 1 በግልጽ ተደንግጓል። ማንኛውም የንግድ ድርጅት በዓመት ውስጥ ያገኘው ትክክለኛ ትርፍ ለግብር አስገቢው መስሪያ ቤት የማሳወቅ ግብር የመክፈል ኃላፊነት እንዳለበትና ይህንን ኃላፊነቱን በመጣስ በተለይም አሳሳች የሆኑ ማስረጃዎችን በማቅረብ ግብር የማጭበርበር ተግባር ከፈጸመ በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆን ከአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 96 እና አንቀጽ 97(1) ድንጋጌዎች ተደንግጓል። አንደኛ ተከሳሽ በ1997ዓ.ም .06 /አንድ መቶ ሰላሳ ሁለት ስድስት መቶ ሰባ ሶስት ብር ከዜሮ ስድስት ሳንቲም/ ከንግድ ስራ ትርፍ አግኝቶ እንደነበር ነገር ግን አንደኛ ተከሳሽ በሕግ አግባብ ላልተቀላቀለው ሜጋ ማስታወቂያ ሰራተኞች የከፈለውን ደመወዝ በስልክ ክፍያና የነዳጅ ወጭ አንደኛ ተከሳሽ ለእራሱ ስራ ያወጣው ህጋዊ ወጭ አስመስሎ በማቅረብና 1997ዓ.ም ከንግድ ስራ ትርፍ እንዳላገኘና ኪሳራ እንደደረሰበት ለተጠሪ ያሳወቀ መሆኑ ተጠሪ ባቀረበው የጽሑፍና የሰው ማስረጃ ተረጋግጧል። ከዚህ በተጨማሪ አንደኛ ተከሳሽከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም ባከናወነው ግብይት .03 /አራት መቶ ሃያ ስድስት ሺ ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ብር ከዜሮ ሶስት ሳንቲም/ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብስቦ ለተጠሪ ይህንን ተጨማሪ እሴት ታክስ ገንዘብ የሰበሰበ መሆኑን እንዳላሳወቀና ገንዘቡንም ገቢ እንዳላደረገ ተጠሪ ባቀረባቸው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች የተረጋገጠ መሆኑን ፍሬ ጉዳይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ስልጣን ባላቸው ፍርድ ቤቶች ተረጋግጧል። ሕግን በመጣስ የሰበሰበውን ታክስ ያላሳወቀ ወይም የሚፈለግበትን ታክስ ያልከፈለ እስከ አምስት አመት ላቀጣ የሚችል መሆኑ በአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 49 የተደነገገ ሲሆን የንግድ ድርጅት ይህንን አዋጅ በመተላለፍ ለሚፈጸመው ጥፋት የወንጀል ተጠያቂነት የሚኖርበት ስለመሆኑ ከአዋጁ ድንጋጌዎች ለመረዳት ይቻላል።
12 .በስር አንደኛ ተከሳሽ የነበረው የንግድ ድርጅት ለልላ ድርጅት ሰራተኞች ሜጋ ማስታወቂያ ሰራተኞች የከፈለውን ደመወዝና የስልክ ወጭ የንግድ ተግባሩን ሲያከናውን ያወጣው ወጭ መሆኑን በሚገልጽ መንገድ ለግብር አስገቢው መስሪያ ቤት ሪፖርት በማቅረብ 1997ዓ.ም ትርፍ አግኝቶና ካገኘውም ትርፍ 39,801.32 የንግድ ስራ ትርፍ ገቢ ግብር መክፈል ሲገባው ኪሳራ እንደደረሰበት አድርጎ ሪፖርት ማቅረቡና ይህም ሪፖርት ለልላ ንግድ ድርጅት ወጭ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ለመሸፈን የወጣ ወጭ እንደ ሕጋዊ ወጭ በማቅረብ የተፈጸመ መሆኑ በኦዲት የተረጋገጠ መሆኑን እንደዚሁም አንደኛ ተከሳሽ ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም የሰበሰበውን ተጨማሪ እሴት ታክስ ለተጠሪ ያላሳወቀና ገንዘቡንም ገቢ ያላደገረገ መሆኑ ተረጋግጧል።
13 .አመልካች 1997ዓ.ም አንደኛ ተከሳሽ ትርፍ አግኝቶ እያለ ትርፍ እንዳላገኘና ኪሳራ እንደደረሰበት ሪፖርት በማድረግ በአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 96 እና አንቀጽ 97 (1) (ሀ) የተመለከቱትን የወንጀል ድርጊቶች ሲፈጽም የአንደኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ የነበረ መሆኑ በተጣራ ማስረጃ ብቻ ሳይሆን አመልካች ባቀረባቸው የመከላከያ ማስረጃዎች የተረጋገጠ መሆኑ የበታች ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ያሳያል። አንደኛ ተከሳሽ ከላይ የጠቀስናቸውን ድንጋጌዎች በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመ መሆኑ ከተረጋገጠ ስራ አስኪያጁ በወንጀሉ ተጠያቂ እንደሚሆን በአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 102 ንዑስ አንቀጽ 1 ተደንግጓል። እንደዚሁም አንደኛ ተከሳሽ በአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 49 የተመለከተውን በመተላለፍ ከ1996 ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ባከናወነው ግብይት የሰበሰበውን ተጨማሪ እሴት ታክስ ለተጠሪ ያላሳወቀና ገንዘቡንም ገቢ ያላደረገ መሆኑ ተረጋግጧል። አንደኛ ተከሳሽ የአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 49 ድንጋጌ የሚጥስ የወንጀል ተግባር በፈጸመበት ጊዜ አመልካች የአንደኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ እንደነበር በተጣራ ማስረጃ ብቻ ሳይሆን አመልካች ባቀረባቸው የመከላከያ ማስረጃዎች ተረጋግጧል።
አንደኛ ተጠሪ ወንጀሉን የፈጸመው ከ1996ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በመሆኑ አመልካች የአንደኛ ተከሳሽ ሂሳብ በተጠሪ በሚጣራበት 2003ዓ.ም እኔ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አልነበርኩም በማለት የሚያቀርበው ክርክር አንደኛ ተከሳሽ በስራ አስኪያጅነት በሚሰራበት ወቅት ለተፈጸመው ወንጀል በአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 56 ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት ተጠያቂ መሆኑን የሚያስቀር ባለመሆኑ የአመልካች ክርክር ተቀባይነት ያለው አይደለም።
14 .የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ከክርክሩ ውጭ እንዲሆን አላደረገም። የስር ፍርድ ቤት ተጠሪ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ እና በአመልካች ላይ የቀረበውን የወንጀል ክስ እና ማስረጃ ከሰማና የአመልካችን መከላከያ ከመረመረ በኋላ ‘’ስለሆነም ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ የሚያስተባብል ማስረጃ ያላቀረቡ በመሆኑ በ1997ዓ.ም 1ኛ ተከሳሽ ባከናወነው የንግድ እንቅስቃሴ ገቢን አሳውቆ ባለመክፈልና ተከሳሾች አሳሳች መረጃ በመስጠትና ኪሳራ ሪፖርት በማድረግና ከ1996ዓ.ም እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ የተሰበሰበውንየተጨማሪ እሴት ታክስ የሰበሰቡትን በሙሉ ሪፖርት ባለማድረጋቸው ሁለተኛው ተከሳሽ (አመልካች) በስራ አስኪያጅነታቸው አንደኛ ተከሳሽ ለፈጸመው ድርጊት ተጠያቂ በመሆናቸው ተከሳሾች በአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 96 እና አንቀጽ 97 ንዑስ አንቀጽ 3 (ሀ) አንደዚሁም በአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 49 ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ ጥፋተኛ ናቸው’’ በማለት ውሳኔ እንደሰጠ ከስር ፍርድ ቤት ከሰጠው ፍርድ በስምንተኛው ገጽ በአራተኛው ፓራግራፍ በግልጽ ሰፍሯል።
15 ይህም የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ከላይ በገለጽናቸው አዋጆች የተመለከቱትን የሕግ ድንጋጌዎችና በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 1 የተደነገገውን በመተላለፍ ወንጀል የፈጸመ መሆኑን በማረጋገጥ የጥፋተኛነት ውሳኔ የሰጠ መሆኑንና አንደኛ ተከሳሽ ወንጀሉን በሚፈጽምበት ጊዜ ሁለተኛ ተከሳሽ አመልካች የአንደኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 286/1994 አንቀጽ 102 እና የአዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 56 ድንጋጌዎች መሰረት ሜጋ ኪነጥበባት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በስራ አስኪያጅነት ሲመራ በነበረበት ጊዜ በድርጅቱ ለተፈጸመው ወንጀል በኃላፊነት የሚጠየቅ መሆኑን በማረጋገጥ የተሰጠ ውሳኔ ነው። ከዚህ አንጻር ሲታይ አመልካች የንግድ ድርጅቱ ወንጀሉን የፈጸመ መሆኑ ሳይረጋገጥ አና ለወንጀሉ ኃላፊ ተብያለሁ በማለት የሚያቀርበው ክርክር በመዝገቡ ያለውን እውነታ የሚያንጸባርቅ ሆኖ አላገኘነውም። አንደኛ ተከሳሽ ከአመልካች ጋር ለተፈጸመው ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ መሆኑን የስር ፍርድ ቤት በመዝገብ ታህሳስ 19 ቀን 2004ዓ.ም በሰጠው ፍርድ በግልጽ የሚታይ ነው።
16 አመልካች የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽን በአግባቡ ሳይጠራ አንደኛ ተከሳሽ በክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን ወይም ጉዳዩ አንደኛ ተከሳሽ በልለበት እንዲታይ ትእዛዝ ሳይሰጥ የወንጀል ክሱን ሰምቶ የወሰነ መሆኑ የሕግ ስህተት ያለበት መሆኑን መከራከሪያ አድርጎ አቅርቧል። አመልካች ከ 2003ዓ.ም ጀምሮ የአንደኛ ተከሳሽ ስራ አስኪያጅ እንዳልሆነና አንደኛ ተከሳሽንም ወክሎ ክርክር ለማቅረብ እንደማይችል በስር ፍርድ ቤት የገለጸ መሆኑን ግራ ቀኙ ካቀረቡት ክርክር ተገንዝበናል። አንደኛ ተከሳሽ የወንጀል ጉዳይ የታየው የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ አንቀጽ 162 አንቀጽ 167 እና ልሎች ድንጋጌዎች ከሚደነግጉት ውጭ ነው ብሎ ካለ የስር ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ በልለበት አይቶ የሰጠው ፍርድ እንዲነሳለት ከሚያመለክት በስተቀር አንደኛ ተከሳሽ በልለበት ታይቶ መወሰኑን አመልካች መከራከሪያ አድርጎ ላያቀርብ የሚችል አይደለም። አንደኛ ተከሳሽ በመወከልም አንደኛ ተከሳሽ በልለበት ታይቶ የተሰጠው ፍርድ እንዲነሳ ለመከራከር የሚያስችለው ውክልና ወይም ስልጣን የለውም ስልጣንም ቢኖረው ክርክሩ መቅረብ የሚገባው በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ሕግ ከአንቀጽ 197 እስከ አንቀጽ 102 የተደነገጉትን ድንጋጌዎች መሰረት በማድረግ መሆን የሚገባው በመሆኑ አመልካች ያቀረበው ክርክር የሕግ መሰረት ያለው ሆኖ አላገኘነውም።
17 አንደኛ ተከሳሽ አግባብነት ባላቸው የንግድ ህግ ድንጋጌዎች መሰረት መፍረሱ ወይም ከልላ ድርጅት ጋር መቀላቀሉን የሚያሳይ ማስረጃ አልቀረበም። ይህም አንደኛ ተከሳሽ ሕጋዊ ህልውና ያለው ድርጅት መሆኑን ያሳያል። አንደኛ ተከሳሽ በህግ አግባብ ሳይፈርስ ወይም ልላ ድርጅት ጋር ተቀላቅሎ ህጋዊ ህልውናውን ሳያጣ አንደኛ ተከሳሽ በእውን እንዳይኖር የፈጸመበትን የንግድ ዓላማ የማይፈጽምና ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዳያደግ በማድረግ በቁሙ ማክሰም የሚቻል መሆኑና አመልካችም አንደኛ ተከሳሽ በህግ አይን የፈረሰ ድርጅት ነው ባይባልም በእውኑ ዓለም የልለና የከሰመ ድርጅት ነው የሚል መከራከሪያ ያቀረቡ መሆኑን ተረድተናል። በመሰረቱ አንድን ድርጅት በቁሙ አንዲከስም በማድረግ ድርጅቱ ህጋዊ ህልውና ኖሮት ተግባራዊ የንግድ እንቅስቃሴ ሲያደርግ በነበረበት ጊዜ ለተፈጸመ ወንጀል የንግድ ድርጅቱንም ሆነ በወቅቱ ወንጀሉ በተፈጸመበት ጊዜ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ የነበረውን ሰውና የልሎች ሰራተኞች የወንጀል ተጠያቂነት ለማስቀረት አይቻለም። ከዚህ በተጨማሪ ሕጋዊ ህልውና ያለው ድርጅት ወንጀል እንዳደረገ ተቆጥሮ የሚቀጣው በሃላፊዎቹ ወይም ከሰራተኞች አንዱ ከድርጅቱ ስራ ጋር በተያያዘ ሁኔታ የድርጅቱን ጥቅም በሕገ ወጥ መንገድ ለማራመድ በማሰብ ወይም የድርጅቱን ህጋዊ ግድታ በመጣስ ወይም ድርጅቱን በመሳሪያነት አላግባብ በመጠቀም በዋና ወንጀል አድራጊነት በአነሳሽነትና በአባሪነት ወንጀል ሲያደርግ መሆኑ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 2 በግልጽ የተደነገገ መርህ ነው። አንድ የንግድ ድርጅት የወንጀል ተግባር ከፈጸመና ጥፋተኛ መሆኑ በፍርድ ከተረጋገጠ በኋላ ድርጅቱ የወንጀሉን ፍርድ ላፈጽም የማይችልበት ሁኔታ በቁም እንዲከስም መደረጉ ለወንጀሉ አድርጎት ኃላፊ የሚሆኑትን ሰራተኞችና ኃላፊዎች በወንጀል ከመጠየቅ ነጻ የማያወጣ በመሆኑ የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በአመልካች ላይ የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የለበትም በማለት በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕግ ቁጥር 195 ንዑስ አንቀጽ 2 (ለ) 2 መሰረት ወስነናል።
የፍድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና የፍድረል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጡት የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 195 ንዑስ አንቀጽ 2(ለ)2 መሰረት በድምጽ ብልጫ ጸንቷል።
መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ።
No topics extracted.