ገዢ የገዛው እቃ ላይ ጉድለት ያለበት ከሆነ ጉድለቱን ለሻጩ ባሳወቀ በአንድ አመት ውስጥ ጉድለቱ እንዱስተካከልለት ክስ ካላቀረበ ክሱ በይርጋ እንደሚታገድ የተደነገገ ቢሆንም ሻጩ እቃውን ወይም የሚሸጠውን ነገር ለገዢ በሚሸጥበት ወይም በሚያስረክብበት ወቅት እቃው ጉድለት ያለበት መሆኑን እያወቀ ጉድለት እንደላለ አድርጎ ወይም ጉድለቱ እንዲይታወቅ አድርጎ በማጭበርበር ለገዢ መሸጡ ወይም ማስረከቡ ከተረጋገጠ ክስ የማቅረቢያ ጊዜው በአንድ አመት ይርጋ የማይገደብ ሲሆን በተቃራኒው ሻጩ በሽያጭ ወይም በርክክብ ወቅት የፈጸመው የማጭበርበር ኦዱት ሰርቪስ ኮርፕሬሽን እና ፀጋ ረታ አስመጪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር 104 ከላለ ጉድለቱን ገዢው ለሻጭ ባሳወቀ በአንድ አመት ውስጥ ክስ ካላቀረበ ክሱ በይርጋ የሚታገድ ስለመሆኑ የፍ/ሕ/ቁ (1) የፍታብሄር ሕግ ቁ ድንጋጌ አላማ ሻጩ በፈጸመው የማጭበርበር ተግባር የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአንድ አመት ውስጥ ክስ አልቀረበም በሚል በወንጀል ድርጊቱ ተጠቃሚ እንዲይሆን ለመከላከል ሲሆን ይህ ማለት ግን የማጭበርበር ድርጊት ከተፈጸመ ምንም አይነት የክስ ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ አይኖረውም ማለት ሳይሆን የማጭበርበር ድርጊቱ እንደ ይርጋ ማቋረጫ ጊዜ ተወስድ የአንድ አመቱ የይርጋ ጊዜ የማጭበርበር ድርጊቱ ከተፈጸመ ጊዜ ጀምሮ እንደ አዱስ መቁጠር የሚጀምር ስለመሆኑ የሻጭ አጭበርባሪነት የሚለው አገላለጽ ምን አይነት እና መቼ የሚፈጸም የሻጩን ድርጊት የሚያመለክት ነው የሚለው በተመለከተ በፍ/ህ/ቁ ሻጩ የሸጠውን ነገር ጉድለቶች ያለበት መሆኑን ገዢው እንዲያውቃቸው በተንኮል ደብቋቸው ከሆነ ሻጩን ከሀላፉነት የሚያድኑ የውል ቃልች ቢኖሩ ሻጩ ከተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይችል የሚያመለክትና ይህም ማለት ሻጩ ለገዢ በሸጣቸው ነገሮች ላይ ጉድለት መኖሩን እያወቀ በተንኮል በሽያጭ ወቅት ምንም አይነት ጉድለት እንደላለባቸው አስመስል ከሸጠ ወይም ከሽያጭ በኋላም ቢሆን ጉድለቱ እንዲይታወቅ ለማድረግ ሻጩ የማጭበርበር ድርጊት የፈጸመ በመሆኑ ተጠያቂ የማያደርገው የውል ቃል እንኳን ቢኖር ውለ ተፈጻሚ የማይሆን እና ሻጩ በኃላፉነት እንደሚጠየቅ የሚያመለክት ስለመሆኑ የፍ/ሕ/ቁ እና የፍ/ህ/ቁ /1
No summary available.
ቀን፡- 05/02/2014 ዓ.ም ዳኞች፡- ብርሀኑ አመነው ተሾመ ሽፈራው ሀብታሙ እርቅይሁን ብርሀኑ መንግስቱ ነፃነት ተገኝ አመልካች፡- ኦዱት ሰርቪስ ኮርፕሬሽን - ጠበቃ መኮንን ይማም - ቀረቡ ተጠሪ፡- ፀጋ ረታ አስመጪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር - አልቀረቡም **
መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል።
**
ክርክሩ የሽያጭ ውልን መነሻ ያደረገ ሲሆን ጉዲዩ በተጀመረበት የፍደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል።
አመልካች የካቲት 4 ቀን 2011 ዓ.ም ባቀረበው ክስ አመልካች የኮምፑዩተር እቃዎችን ለመግዛት ባወጣው ጨረታ ተጠሪ አሸንፍ እቃዎቹን አቅርቦ ክፍያ የተቀበለ ቢሆንም እቃዎቹን ከሰርቨሩ ጋር የሚያገናኙ ኬብልችን ባለማቅረቡ ምክንያት እቃዎቹ የተፈለገውን አገልግልት መስጠት አልቻለም።
በመሆኑም ኬብልቹን እንዱያቀርብ ወይም በወቅቱ የገበያ ዋጋ የእቃዎቹን ግምት ብር 182,900 ወጪና ኪሳራን ጨምሮ እንዱከፍል ይወሰንልኝ በማለት ዲኝነት ጠይቋል።
ተጠሪ የካቲት 29 ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ መልስ አመልካች እቃዎቹ ጉድለት ያለባቸው መሆኑን ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በ1 አመት ውስጥ ክስ ስላላቀረበ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል የሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል።
ፍርድ ቤቱም በመቃወሚያው ላይ ግራ ቀኙን አከራክሮ ግንኙነታቸው የሽያጭ ውልን መሰረት ያደረገ ስለሆነ ለጉዲዩ ተፈፃሚነት ያለው ስለውልች በጠቅላላው የተደነገገው የፍ/ሕ/ቁጥር 1845 ሳይሆን የሽያጭ ውልን የሚመለከተው የፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) ነው። በዚህ ድንጋጌ መሰረትም በሻጩ አጭበርባሪነት ካልሆነ በቀር ገዢው ጉድለቱን ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ ክስ ማቅረብ አለበት። አመልካች የተጠሪ አጭበርባሪነት ያለበት ስለመሆኑ በክሱ ያልገለፀ ሲሆን ተጠሪው የእቃዎቹን ጉድለት እንዱያስተካክል ያሳወቀው ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም እንዱሁም ለተረከባቸው እቃዎች ክፍያ የፈጸመው ጥቅምት 25 ቀን 2009 ዓ.ም በመሆኑ ክሱ የቀረበው ሁለት ኣመት ካለፈው በኋላ የካቲት 4 ቀን 2011 ዓ.ም ነው። የተጠሪ ሰራተኛ ሰኔ 10 ቀን 2009 ዓ.ም UPS 5kg ለቼክ አፔ መውሰደ ጉድለቱን በግልፅ አምኗል አያስብልም። አምኗል ቢባል እንኳ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በ1 ዓመት ውስጥ ክሱ ስላልቀረበ በይርጋ ይታገዲል በማለት ብይን ሰጥቷል።
አመልካች ውሳኔውን በመቃወም ይግባኙን ለፋደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ያቀረበ ቢሆንም የስር ፍ/ቤት ውሳኔን በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰረት በማፅናቱ ጥቅምት 13 ቀን 2013 ዓ.ም የተፃፈ የሰበር አቤቱታውን አቅርቧል። የአቤቱታው ይዘት ባጭሩ አመልካች በክሱ ላይ ፍሬ ነገርን ከመግለፅ በዘለለ ተጠሪው መቃወሚያ ሉያቀርብ ይችላል ብል በማሰብ በክስ መስማት ወቅት ሉያቀርብ የሚችለውን መከራከሪያ አስቀድሞ ማቅረብ ግዳታ በላለበት ተጠሪው የማታለል እና የማጭበርበር ተግባር ስለመፈፀሙ አመልካች በክሱ አልገለፀም መባለ ተገቢ አይደለም። ተጠሪ እቃዎቹን አስተካክላለው ብል መውሰደን አልካደም። የወሰደውም እቃውን ባስረከበ በአንድ ዓመት ውስጥ ሲሆን እቃውን በእምነት በመውሰድ በተግባር የማታለል እና የማጭበርበር ተግባር የፈፀመ ሲሆን እቃዎቹን አስተካክል የሚያቀርብበት ጊዜም ስላልተወሰነ እና እቃዎቹን አስተካክል እንዱያስረክብ በተደጋጋሚ በአመልካች ሲጠየቅ ከዛሬ ነገር አስተካክዬ እመልሳለው ማለቱ ስላልተካደ አስፈላጊ ከሆነም ምስክሮቻችንን በመስማት ሉጣራ ሲገባ ክሱ በይርጋ ይታገዲል መባለ ተገቢ አይደለም። ውለ የሽያጭ ብቻ ሳይሆን የጥገና ማደስና መለዋወጫ ማቅረብ መሆኑ በሰነድ ተረጋግጦ እያለ ሽያጭ ብቻ ነው ተብል የሽያጭ ሕግ የይርጋ ድንጋጌ ተግባራዊ መደረጉ እንዱሁም እቃው በተጠሪ እጅ ያለ በመሆኑ አመልካች በማንኛውም ጊዜ ንብረቱን መጠየቅ የሚችል ሁኖ እያለ ክሱ በይርጋ ይታገዲል መባለ የፍ/ሕ/ቁጥር 1206 እና የፍደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት በመ/ ቅፅ 10 የሰጠውን ውሳኔ የሚቃረን መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው የሚል ነው።
አቤቱታው በአጣሪ ችልቱ ተመርምሮ ተጠሪ የእቃውን ጉድለት አምኖ መልሶ መቀበለን ለክሱ በሰጠው መልስ አምኖ እያለ ክሱ በአንድ አመት ይርጋ ይታገዲል ተብል የመወሰኑን አግባብነት ከፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) እና አግባብነት ካላቸው የሕግ ድንጋጌዎች ጋር አገናዝቦ ለመመርመር ያስቀርባል በመባለ ተጠሪ መልሱን እንዱያቀርብ ታዟል።
ተጠሪም ጥር 10 ቀን 2013 ዓ.ም የተፃፈ መልስ አቅርቧል። የመልሱ ይዘት ባጭሩ ተጠሪ ለክሱ በአማራጭ በሰጠው መልስ አመልካች የመለሳቸውን እቃዎች አስመልክቶ ክትትል አላደረገም በሚል መቀመጡ አማራጭ ክርክር ከሚሆን በቀር በፍ/ሕ/ቁጥር 1851(ሀ) መሰረት እዲውን አምኗል አያስብልም። እቃው ጉድለት አለበት በሚል ማሳወቅም ሆነ ጉድለት አለ በሚል እቃ መመለሱ መታመኑ በውጤት ደረጃ አንድ ስለሆነ በፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) መሰረት አመልካች በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ክስ ስላላቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዲል መባለ ተገቢ መሆኑን የሚገልፅ ነው።
አመልካች የካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም የተፃፈ የመልስ መልሱን ያቀረበ ሲሆን የሰበር አቤቱታውን በማጠናከር ተከራክሯል።
የክርክሩ አመጣጥ ባጭሩ ከላይ የተመለከተው ሲሆን የአመልካች ክስ በይርጋ ይታገዲል ተብል የመወሰኑን አግባብነት በስር ፍ/ቤት ከተደረጉ ክርክሮች፣ በማስረጃ ከተረጋገጡ ፍሬ ነገሮች እንዱሁም ለጉዲዩ ተገቢነት ካላቸው የሕግ ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ እንደሚከተለው መርምረነዋል።
እንደመረመርነውም አመልካች በዋናነት የሚከራከረው ተጠሪው ክርክር ያስነሳውን እቃ መልሶ መረከቡ እና በተለያዩ ጊዜያትም ከዛሬ ነገ አስተካክዬ አስረክባለው እያለ እንደነበር ባልተካደበት አስፈላጊ ከሆነም ምስክር ሉሰማ ሲገባ እንዱሁም ውለ ሽያጭ ብቻ ሳይሆን የጥገና እና የመለዋወጫ እቃ አቅርቦት ጭምር ሆኖ እያለ ክሱ በአንድ አመት ይርጋ ይታገዲል መባለ ተገቢ አይደለም በማለት ነው። ተጠሪ በበኩለ እቃውን መልሶ መቀበለን በአማራጭ ክርክር ማቅረቡ እዲውን አምኗል የማያስብል እና አመልካች ጉድለት አለበት በሚል ማሳወቁም ሆነ እቃውን መመለሱ በውጤት ደረጃ ልዩነት ስለላለው ክሱ በፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) መሰረት በይርጋ ይታገዲል ተብል መወሰኑ ተገቢ መሆኑን ገልፆ ተከራክሯል።
ገዢው ክስ ማቅረቡን የከለከለው የሻጩ አጭበርባሪነት ካልሆነ በቀር እቃው እንደ ውለ ትክክል አለመሆኑን ወይም ጉድለት ያለበት መሆኑን ካስታወቀበት ቀን አንስቶ እስከ አንድ አመት ውስጥ ክስ ያላቀረበ እንደሆነ እቃው ጉድለት አለበት ወይም እንደ ውለ የቀረበ አይደለም በማለት ክስ ማቅረብ የማይችል መሆኑ በፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) ላይ ተመላክቷል። ይህም ማለት አንድ ገዢ የገዛው እቃ ላይ ጉድለት ያለበት ከሆነ ጉድለቱ ለሻጩ ባሳወቀ በአንድ አመት ውስጥ ጉድለቱ እንዱስተካከልለት ክስ ካላቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዲል። ነገር ግን ገዢው በዚህ አንድ አመት ውስጥ ክስ እንዲያቀርብ የሻጩ አጭበርባሪነት ከልክልት ከሆነ ገዢው ጉድለት መኖሩን ካሳወቀ ከአንድ አመት በኋላም ቢሆን ጉድለቱ እንዱስተካከልለት ክስ ማቅረብ ይችላል። በልላ አባባል የሻጩ የማጭበርበር ድርጊት የአንድ አመቱን የይርጋ ጊዜ ገደብ የሚያቋርጥ ምክንያት ይሆናል። የዚህ ድንጋጌ አላማ ሻጩ በፈጸመው የማጭበርበር ተግባር የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአንድ አመት ውስጥ ክስ አልቀረበም በሚል በወንጀል ድርጊቱ ተጠቃሚ እንዲይሆን ለመከላከል ነው። ይህ ማለት ግን የማጭበርበር ድርጊት ከተፈጸመ ምንም አይነት የክስ ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ አይኖረውም ማለት አይደለም። የማጭበርበር ድርጊቱ እንደ ይርጋ ማቋረጫ ጊዜ ተወስድ የአንድ አመቱ የይርጋ ጊዜ የማጭበርበር ድርጊቱ ከተፈጸመ ጊዜ ጀምሮ እንደአዱስ መቁጠር የሚጀምር ይሆናል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ላላው መታየት ያለበት የሻጩ አጭበርባሪነት የሚለው አገላለጽ ምን አይነት እና መቼ የሚፈጸም የሻጩን ድርጊት የሚያመለክት ነው? የሚለው ላሆን ይገባል። በፍ/ህ/ቁጥር 2297 ሻጩ የሸጠውን ነገር ጉድለቶች ያለበት መሆኑን ገዢው እንዲያውቃቸው በተንኮል ደብቋቸው ከሆነ ሻጩን ከሀላፉነት የሚያድኑ የውል ቃልች ቢኖሩ ሻጩ ከተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይችል ያመለክታል። ይህም ማለት ሻጩ ለገዢ በሸጣቸው ነገሮች ላይ ጉድለት መኖሩን እያወቀ በተንኮል በሽያጭ ወቅት ምንም አይነት ጉድለት እንደላለባቸው አስመስል ከሸጠ ወይም ከሽያጭ በኋላም ቢሆን ጉድለቱ እንዲይታወቅ ለማድረግ ሻጩ የማጭበርበር ድርጊት የፈጸመ በመሆኑ ተጠያቂ የማያደርገው የውል ቃል እንኳን ቢኖር ውለ ተፈጻሚ እንደማይሆን እና ሻጩ በኃላፉነት እንደሚጠየቅ የሚያመለክት ነው። የፍ/ህ/ቁጥር 2298/1 የፍ/ሕ/ቁጥር 2297 ተከታይ እንደመሆኑ ተጣምረው ሲነበቡ ሻጩ እቃውን ወይም የሚሸጠውን ነገር ለገዢ በሚሸጥበት ወይም በሚያስረክብበት ወቅት እቃው ጉድለት ያለበት መሆኑን እያወቀ ጉድለት እንደላለ አድርጎ ወይም ጉድለቱ እንዲይታወቅ አድርጎ በማጭበርበር ለገዢ መሸጡ ወይም ማስረከቡ ከተረጋገጠ ክስ የማቅረቢያ ጊዜው በአንድ አመት ይርጋ የማይገደብ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው። በተቃራኒው ሻጩ በሽያጭ ወይም በርክክብ ወቅት የፈጸመው የማጭበርበር ድርጊት ከላለ ጉድለቱን ገዢው ለሻጭ ባሳወቀ በአንድ አመት ውስጥ ክስ ካላቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዲል ማለት ነው።
በተያዘው ጉደይ አመልካች ተጠሪው ከዛሬ ነገ እቃውን እጠግናለው በማለት የማጭበርበር ተግባር ስለፈጸመ ክሱ በይርጋ ተቋርጧል መባለ ተገቢ አይደለም በማለት የሚከራከር ቢሆንም ከላይ እንደተገለጸው በፍ/ሕ/ቁጥር 2298(1) የተገለፀው የማጭበርበር ተግባር እቃውን ከሚመለከት ዝርዝር መግለጫ ወይም በግብይቱ ጊዜ እቃው ጉድለት ያለበት መሆኑ እየታወቀ ይህን በመደበቅ ከተፈጸመ ተግባር ጋር የሚገናኝ ነው። ተጠሪ ከዛሬ ነገ እቃውን አስተካክላለሁ እያለ ቆይቶ ቢሆን እንኳን ተጠሪ የዋቢነት ሃላፉነቱን አለመወጣቱን የሚያሳይ እንጂ በግዢ ወቅት በእቃው ላይ ያለው ጉድለት በአመልካች እንዲይታወቅ የማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙን የሚያመለክት አይደለም። ከግብይቱ በኋላ የተጠሪ ሰራተኛ ሰኔ 10 ቀን 2009 ዓ.ም UPS 5kg ለቼክአፔ መውሰደ ጉድለቱን በግልፅ አምኗል የሚያስብል ካለመሆኑም በላይ ተጠሪ ጉድለቱን ለማስተካከል እቃውን ተቀብሎል ቢባል እንኳ በዚህ አግባብ ባለማስተካከለ አመልካች ተጠሪ እቃውን ለማስተካከል ከተቀበለበት ጊዜ ጀምሮ በሕግ በተገለፀው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ክስ በመመስረት ዲኝነት ሉጠይቅ ይገባ ነበር። ከዚህ ጋር ተያይዞ አመልካች ተጠሪው ከዛሬ ነገ እቃውን አስተካክላለው በማለት ያጭበረበረኝ ስለመሆኑ ምስክሮቼ መሰማት ነበረባቸው በማለት የሚከራከር ቢሆንም በፍትሐብሄር ክርክር ማስረጃ የሚሰማው እና ፍሬ ነገር እንዱነጥር የሚደረገው ለጉዲዩ አወሳሰን የግድ አስፈላጊ ሲሆን ብቻ ስለመሆኑ ከፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል። ስለሆነም አመልካች ምስክሮቼ ሉሰሙ ይገባ ነበር በማለት የሚያቀርበው ቅሬታ ተገቢነት የለውም።
በመጨረሻም አመልካች ለክሱ መነሻ ያደረገው የገዛዋቸው እቃዎች በውለ መሰረት ተሟልተው የቀረቡ ባለመሆኑ ተገቢውን አገልግልት መስጠት አልቻለም የሚል ሁኖ እያለ እና ውላችን የጥገና እና የመለዋወጫ አቅርቦትን ስለሚጨምር የፍ/ሕ/ቁጥር 2298 ለጉዲዩ ተፈጻሚነት የለውም በማለት የሚያነሳው መከራከሪያ ተገቢነት ስንመለከት አመልካች በስር ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ ተጠሪው ጥገና እንዱያደርግልኝ ይወሰንልኝ የሚል ግልጽ ዲኝነት አልጠየቀም። አመልካች በስር ፍርድ ቤት ከመለዋወጫ እና ጥገና ውል ጋር የተያያዘ ክስ ባላቀረበበት የተጠቀሰው የይርጋ ድንጋጌ ተፈጻሚ ላሆን አይገባም በሚል የሚያቀርበው መከራከሪያ ተቀባይነት ያለው አይደለም። አመልካች በስር ፍርድ ቤት ክስ ያቀረበው የሽያጭ ውልን መሰረት አድርጎ በተሸጠው እቃ ላይ አለ የሚለው ጉድለት በገንዘብ ወይንም በአይነት እንዱስተካከልለት በመሆኑ ለጉዲዩ የፍ/ሕ/ቁጥር 2298/1 ተፈጻሚነት ይኖረዋል።
በመሆኑም አመልካች ተጠሪ እቃውን እንዱያስተካክል ያሳወቀው ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም መሆኑ እና ክሱ የቀረበው የካቲት 1 ቀን 2011 ዓ.ም መሆኑ ተረጋግጦ በይርጋ ይታገዲል ተብል በስር ፍ/ቤቶች በተሰጠው ብይን ላይ እና ብይኑን በማጽናት በተሰጠው ውሳኔ ላይ የተፈፀመ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የለም በማለት ተከታዩን ወስነናል።
የፍደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በኮ/መ/ ግንቦት 16 ቀን 2011 ዓ.ም የሰጠው ብይን እንዱሁም የፍደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በኮ/መ/ ሐምል 22 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችልት ሰጠው ውሳኔ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348(1) መሰረት ፀንቷል።
በዚህ ችልት የተደረገው ክርክር ያስከተለውን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የራሳቸውን ይቻለ።
አመልካች ለተጠሪ እንዱስተካከል ሰጥቻለሁ የሚለውን እቃ በተመለከተ ባለበት ሁኔታ ለማስመለስ ክስ ከማቅረብ ይህ ውሳኔ አያግደውም።
ሄ/መ
No topics extracted.