No summary available.
መጋቢት 21 ቀን 2002 ዓ.ም ዳኞች፡- መንበረፀሐይ ታደሰ ሂሩት መለሰ ብርሃኑ አመነው አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ አመልካች፡- የኢት/መድን ድርጅት ነ/ፈጅ ማህላት አለሙ - ቀረቡ ተጠሪ፡- ወ/ሮ ገነት ስዩም - ቀረቡ መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል።
በዚህ መዝገብ የቀረበው የመድን ሰጪ የክርክር አድማስ አስመልክቶ የኦሮሚያ ብ/ክ/መ/ጠቅላይ ፍ/ቤት የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 43 ጠቅሶ የሰጠው ፍርድ መሰረታዊ የሕግ ስሕተት አለው በሚል ነው።
ለዚህ ሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ክርክር የተጀመረው በኦሮሚያ ብ/ክ/መ/ በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ጣልቃገብ ተከራካሪ ነበር። የተጠሪ የክስ ምክንያት ንብረትነቱ በሥር ፍ/ቤት አንደኛ ተከሳሽ የነበረው ቴስትድ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሆነ መኪና ሰላዲ ቁጥር 3-13690 ኢት. በሥር ሁለተኛ ተከሳሽ እየተሽከረከረ በከሳሽ መኪና ሰላዲ ቁጥር 3-06622 አ/አ ገጭቶ ጉዲት አድርሷል በሚል ለጥገና የወጣ ወጪ እና የተቋረጠ ገቢ እንዱከፍል እንዱወሰን የሚል ሲሆን አንደኛ ተከሳሽ ቀርቦ መድን ሰጪው (አመልካች) በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43 መሰረት ጣልቃ ገብነት እንዱከራከር እንዱታዘዝ አመልክቷል። የከፍተኛው ፍ/ቤትም አመልካች በክርክሩ እንዱገባ ካደረገ በኋላ የግራ ቀኙን ክርክር እና ማስረጃ መርምሮ ፍርድ ሰጥቷል። ከፍተኛው ፍ/ቤት በሰጠው ውሳኔ ተከሳሽ እና ጣ/ገብ አላፉ ናቸው ካለ በኋላ የካሣ መጠን አስመልክቶ ለመኪናው ማስጠገኛ የወጣውን ወጪ ብር 44,451(አርባ አራት ሺህ አራት መቶ ሃምሳ አንድ ብር) እና የተቋረጠ ገቢ በቀን አንድ መቶ(100) ብር ሂሳብ መኪናው ተጠግኖ እስኪጠናቀቅ ጊዜ ድረስ ተሰልቶ እንዱከፈል በማለት ይህንንም ጣልቃገብ (አመልካች) እስከ ብር አንድ መቶ ሺህ (100,000) በመድን ውል በሰጠው ዋስትና መሰረት እንዱሸፍን ቀሪውን አንደኛ ተከሳሽ (ባለንብረት) እንዱከፈል ፈርዶል።
አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር ተሰኝቶ ይግባኙን ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት አቅርቧል።
የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ አመልካች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43(1) መሰረት በተከሳሽ ጠያቂነት ወደ ክርክሩ የገባ መሆኑን በመጥቀስ ጣልቃገብ ከተከሳሹ ጋር ያለውን ኃላፉነት ከመከራከር ውጪ ተከሳሽን ተክቶ ከከሳሽ ጋር መከራከር አይችልም በማለት በአመልካች በኩል ቀርቦ የነበረውን የሕግ እና የፍሬ ነገር ክርክር ሳይመረምር የሥር ፍ/ቤት ውሳኔን አፅንቷል።
አቤቱታ የቀረበለት የኦሮሚያ ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት አመልካች በፋዳራል መንግሥት የተመዘገበ ድርጅት በመሆኑ በአዋጅ 25/88 አንቀጽ 5(6) መሰረት ጉዲዩን ለመዲኘት ሥልጣን የለኝም ሲል አቤቱታውን ባለመቀበል መዝገቡን ዘግቶታል።
ለዚህ የቀረበው የሰበር አቤቱታ በዚሁ ላይ ሲሆን አመልካች የሥር ፍ/ቤቶች የሕግ እና የፍሬ ነገር ስሕተት ያላቸውን ዘርዝሮ አቅርቧል። ይህ ሰበር ሰሚ ችልትም ተጠሪን አስቀርቦ ሰምቷል።
የጉዲዩ አመጣጥ እና የግራ ቀኙ ክርክር በአጭሩ ከፍ ሲል የተመለከተው ሲሆን ጉዲዩን ከሕጉ አገናዝበን መርምረናል። እንደመረመርነውም በዚህ ችልት እልባት ሉያገኝ የሚገባው ጭብጥ የኦሮሚያ ጠ/ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43(1) አተረጓጎም አግባብነት እና የአመልካች የክርክር አድማስ(ወሰን) እስከምን ድረስ ነው የሚለው ሆኖ አግኝተነዋል።
በመሰረቱ አመልካች ወደ ክርክሩ የገባው በሥር ፍ/ቤት ተከሳሽ ከነበረው ባለንብረት ጋር ባለው የመድን ውል መሰረት እንደሆነ ከመዝገቡ መረዲት ችለናል። አንድ ተከሳሽ ከእሱ ጋር ኃላፉነት ሉወስድ ወይም ሉከፈል የሚችል ሦስተኛ ወገን ወደ ክርክሩ እንዱገባለት እንዱታዘዝ ማመልከት እንደሚችል የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43(1) ድንጋጌ ያመለክታል። በዚህ ጥያቄ መነሻ ወደ ክርክሩ እንዱገባ የተደረገ ተከራካሪ ወገን በክርክሩ ውስጥ ሉያነሳ የሚችለው የኃላፉነት እና የኃላፉነት መጠን አስመልክቶ የክርክሩ ዘንግ ከተከሳሽ፣ ከከሳሽ ወይንስ ከሁለቱም ወገን ጋር ላሆን ይገባል የሚለውን ጥያቄ አስመልክቶ በሁለት አቅጣጫ ምላሽ ሉያገኝ እንደሚችል መረዲት ያስፈልጋል። ይኸውም የጣልቃገብ ኃላፉነት ምንጭ ውል ወይንስ ሕግ የሚለው በመሰረታዊ ሕግ ድንጋጌዎች የሚወሰን መሆኑ እና በልላ በኩልም የክርክሩ አቀራረብ እና ይዘት በሥነ-ሥርዓት ሕጉ በተደነገገው አግባብ መሆን እንዲለበት መረዲት ይቻላል።
በተያዘው ጉዲይ የመድን ሰጪ ኃላፉነት መሰረቱ ውል መሆኑ እሙን ነው። መድን ሰጪ የሚኖረው መብት እና ግዳታ በውል የተመለከተ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በመሰረታዊ ሕጉ የተደነገጉትን አስፈላጊ እና አስገዲጅ ሁኔታዎችንም መጠበቅ ያለበት ስለመሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም።
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43(1) መሰረት ወደ ክርክሩ እንዱገባ የተደረገው ሦስተኛ ወገን በክርክሩ ሂደት ሉያነሳ የሚችለው ክርክር ምን ድረስ ነው የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ አስመልክቶ ይህ ሰበር ሰሚ ችልት በመ/ የሰጠውን የህግ ትርጉም መመልከት አግባብ ሆኖ አግኝተናል። በተጠቃሹ መዝገብ ላይ የክርክሩ ተካፊይ ሦስተኛ ወገን የሚያቀርበው ክርክር ሁለት ፈርጅ ሉይዝ የሚችል መሆኑ ተመልክቷል። ይኸውም “አንደኛው ከተከሳሽ ጋር ሆኖ ድርሻ ክፍያ ወይም ስለተከሳሽ ሆኖ የካሣ ክፍያ የመክፈል ግዳታ ያለበት መሆኑን ተቀብል በተከሳሽ እግር በመተካት ተከሳሽ ለከሳሽ ኃላፉነት የማይኖርበት መሆኑን፤ ኃላፉነት አለበት እንኳ ቢባል ሉከፈል በሚገባው የካሣ መጠን ላይ ከከሳሽ ጋር ንጥጥር ማድረግ፤ መሟገት የሚችልበት ክርክር ሲሆን ላላው እና ሁለተኛው ደግሞ ድርሻ ወይም ካሣ ለመክፈል ለተከሳሽ ከህግ ወይም ከውል የመነጨ ግዳታ የለብኝም በማለት መከራከር የሚችልበት መንገድ ነው።” ስለሆነም የድንጋጌው ይዘት ጣልቃገብ ሦስተኛ ወገን ተከሳሽ በክርክሩ ከገባ በኋላ መሟገት የሚችለው ከተከሳሽ ጋር እንጂ ከከሳሽ ጋር ለመከራከር የሚያስችለው መብት የለውም የሚለው ድምዲሜ የሕግ መሰረት የለውም የሚል ትርጉም ሰጥቷል።
የሰበር ሰሚ ችልቱ በመ/ ላይ ይህንን ትርጉም ለመስጠት መሰረት ያደረገው የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ዓላማ እና የሙግት አመራር ውጤታማነት እንዱሁም የድንጋጌ ቁጥር 43(1) እና 76 እንዱሁም የመሰረታዊ ሕጉ ድንጋጌዎች ውስጥ የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1896፣ 1897፣ 1908 እና 1909 አፈጻጸም እንዱሁም በንግድ ሕግ ቁጥር 687,688 እና 683 ድንጋጌዎች በክርክር አመራር ረገድ የሚፈፀሙበትን ሁኔታ እና ግብ መነሻ በማድረግ መሆኑ በፍርደ ሀተታ ተገልጿል።
ለማጠቃለል የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ድንጋጌ ቁጥር 43 አስፈላጊነትም ተከታታይ ክስ ሳይኖር በአንድነት እንዱታይ በማድረግ የኃላፉነት እና መጠኑን እንዱሁም ከፊዩን ወገን በመለየት የመጨረሻ እልባት መስጠት ማስቻል እንደመሆኑ በተለይ ካሣ (indemnity) የመክፈል ግዳታ ያለበት አመልካችን መሰል የመድን ድርጅት ከከሳሹ ጋር ያለውን አጠቃላይ ክርክር ማቅረብ የሚችል ስለመሆኑ በውሳኔው ትርጉም ሰጥቶበታል።
ይህ የሰበር ሰሚ ችልት የሰጠው የሕግ ትርጉም እስካልተለወጠ ድረስ በማናቸውም ድርሻ በሚገኙ ፍ/ቤቶች አስገዲጅነት ያለው ስለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 454/97 አንቀጽ 2(4) ሥር ተደንግጓል። ስለሆነም የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት አመልካች ከተከሳሽ ጋር እንጂ ከከሳሽ ጋር መከራከር አይችልም በማለት የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 43(1) በመጥቀስ የሰጠው ፍርድ በፋዳራለ ሰበር ሰሚ ችልት የተሰጠውን አስገዲጅ የሕግ ትርጉም ያላገናዘበ በመሆኑ ፍርደ መሰረታዊ የህግ ስሕተት የተፈፀመበት ሆኖ አግኝተናል። ስለዚህም አመልካች በክርክሩ ሉያነሳ የሚችለው የኃላፉነት እና የኃላፉነት መጠን ከተከሳሽ ጋር ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ከከሳሽ ጋር ላሆን እንደሚችል የፍ/ብ/ሕግ ድንጋጌ ቁ 43(1) ይዘት እና የሰበር ሰሚ ችልት ትርጉም ያስገነዝባል። በዚሁ መሰረት ተከታዩን ውሳኔ ሰጥተናል።
የኦሮሚያ ጠ/ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት በመ/ መጋቢት 25/2000 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 348(1) መሰረት ተሽሯል።
አመልካች ከከሳሽ ጋር በሕግም ሆነ በፍሬ ነገር ረገድ መከራከር የሚችል በመሆኑ የኦሮሚያ ጠ/ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የይግባኝ መዝገቡን አንቀሳቅሶ ይግባኝ ክርክሩን ተመልክቶ የመሰለውን ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ 343(1) መሰረት የዚህ ውሳኔ ግልባጭ ይድረሰው ብለናል። የዚህን ፍ/ቤት ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻለ።
No topics extracted.