No summary available.
መጋቢት 23 ቀን 2000 ዓ.ም ዳኞች፡- Aብዱልቃድር መሐመድ ደስታ ገብሩ ሂሩት መለሰ ታፈሰ ይርጋ ሡልጣን Aባተማም Aመልካች፡- በቀድሞ ወረዳ 3 ቀበል 07 Aስተዳደር ጽ/ቤት ነ/ፈጅ ገ/ፃዲቅ ቀረቡ ተጠሪዎች፡- Eነ ወ/ሮ ክብርነሽ ቀደመ ወኪል Eመቤት ሣህለማርያም
በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ የጀመረው በA/A ከተማ ነክ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው። ተጠሪዎች በዚሁ ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ የ1ኛ ተጠሪ ባለቤትና የተቀሩት ተጠሪዎች Aባት በወረዳ 5 ቀበል 07 መስተዳድር ክልል ውስጥ ባዶ ቦታ ተከራይተው Aፈር ኪራይ Eየከፈሉ በቦታው ላይ ቤት ሰርተው በማከራየት ሲጠቀሙ ቆይተዋል። Eሣቸው በ1968 ዓ.ም ከሞቱ በኋላም ወራሽነታችንን Aረጋግጠን ለኪራይ ቤቶች Aስተዳደር ድርጅት የAፈር ግብር Eየከፈልን በኋላም ለቀበልው መስተዳደር በዚሁ መልክ Eየከፈልን በውርስ ባገኘነው ሱቅ ስንጠቀም ቆይተናል። የቀበልው መስተዳደር ቤቱን የ1ኛ ተጠሪ ባለቤት Eና የተቀሩት ተጠሪዎች Aባት የሰሩት መሆኑን Eያወቀ በየወሩ ብር 6,160.00 (ስድስት ሺህ Aንድ መቶ ስልሣ) Eንድንከፍል ውል Aስፈርሞናል። በመጨረሻም ነሐሴ 1 ቀን 1993 ዓ.ም. Aዲስ የኪራይ ውል ለ1 ዓመት ካልፈረማችሁ Eያለን ስለሆነ ቀድሞ ስንከፍል የነበረውን ብር 55.00 የAፈር ግብር ብቻ Eየከፈልን በገንዘባችን በሰራነው ቤት ኪራይ Eንድንከፍል ሁከት ይወገድልን። Aላግባብ ያስከፈለንን ብር 24,844.48 (ሃያ Aራት ሺህ ስምንት መቶ Aርባ Aራት ብር ከAርባ ስምንት ሣንቲም) ተመላሽ Eንዲያደርግልን ይወስንልን ሲሉ ጠይቀዋል።
Aመልካችም ለቀረበበት ክስ መቃወሚያና በፍሬ ጉዳዩ ላይ መልስ የሰጠ ሲሆን በበኩሉም የተከሣሽ ከሣሽነት ክስ Aቅርቧል። በክሱም ተጠሪዎች በነበራቸው የተሻሻለ የቤት ኪራይ ውል መሰረት ብር 6,160/ስድስት ሺህ Aንድ መቶ ስልሳ/ Eየከፈሉ ቢቆዩም ከጥር 1994 ዓ.ም. Eስከ Aሁን ድረስ መክፈል ስላቆሙ ውዝፍ ኪራይ ከወለድ ጋር ታስቦ ይክፈሉ። በመሃከላችን ያለው ውል ከነሐሴ 1994 ዓ.ም ስላለቀ ቤቱን ልረከብ በማለት ጠይቋል።
ተጠሪዎችም ለቀረበባቸው የተከሣሽ ከሣሽነት ክስ መልስ ሰጥተው ተከራክረዋል።
ፍ/ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ተመልክቶ ቤቱን የ1ኛ ተጠሪ ባለቤትና የቀሪዎቹ Aባት የሰሩት መሆኑ ተረጋግጧል። በመሆኑም ቀድሞውኑ በግል ቤት ላይ Aስተዳደሩ የኪራይ ውል መዋዋል Aይገባውም ነበር። ስለዚህም ውሉ ሕገ ወጥ ነው። ውሉ ሕጋዊ ባለመሆኑ Aመልካች ተጠሪዎች ኪራይ ይክፈሉ ብሎ ማስገደዱ ሁከት በመሆኑ ሁከቱ ይወገድ። ተጠሪዎች ከመስከረም 1994 ዓ.ም. Eስከ ታህሳስ 1994 ዓ.ም Eንዲከፍሉ የተደረገው ሕገ ወጥ በመሆኑ ይኸው ገንዘብ ይመልስ በማለት ወስኗል።
በዚህ ውሣኔ Aመልካች ቅር ተሰኝቶ ይግባኙን ለከተማ ነክ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ይግባኝ ቢያቀርብም ፍ/ቤቱ የመጀመሪያውን ውሣኔ Aጽንቷል።
የA/A ከተማ ነክ ሰበር ሰሚ ችሎትም ውሣኔው መሰረታዊ የሕግ ስህተት ¾KuƒU በማለት የAመልካችን የሰበር Aቤቱታ ውድቅ Aድርጐታል።
የሰበር Aቤቱታውም የቀረበው የሥር ፍ/ቤቶች ውሣኔ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው። ይህ ችሎትም የኪራይ ውሉ Eንዲፈርስና የኪራይ ገንዘቡ Eንዲመለስ የተሰጠውን ውሣኔ Aግባብነት ለመመርመር Aቤቱታው በሰበር ችሎት ቀርቦ Eንዲታይ Aድርጓል። ተጠሪዎችም Aቤቱታው ደርሷቸው መልስ የሰጡ ሲሆን ችሎቱም ጉዳዩን EንደሚŸ}K¨< መርምሯል።
ከፍ ሲል Eንደተገለፀው በከተማ ነክ መ/ደረጃ ፍ/ቤት ክስ የተመሰረተው ሟች Aቶ ሣህለማሪያም ፈርዳ ባዶ ቦታ ተከራይተው የAፈር ኪራይ Eየከፈሉ በገንዘባቸው በሰሩት ቤት ላይ Aመልካች ኪራይ Eንዲከፍሉ በማድረግ የፈጠረው ሁከት Eንዲወገድ Eና ቀደም ሲል የከፈሉት ገንዘብ Eንዲመለስላቸው ነው። ከክርክሩ ሂደት ተጠሪዎች ከ1988 ዓ.ም ጀምሮ ከAመልካች ጋር የኪራይ ውል ፈጽመው በቤቱ ኪራይ Eየከፈሉ ይኖሩ Eንደነበር ተረድተናል። ተጠሪዎች ክስ ለማቅረብ ምክንያት የሆናቸውም Aመልካቹ ነሐሴ 1993 ዓ.ም በAንድ ዓመት ውል Eንዲፈጽሙ መጠየቁ ነው።
በፍ/ሕ/ቁ 1149/1/ መሰረት ይዞታ የተወሰደበት ወይም በይዞታው ላይ ሁከት የተነሣበት ሰው የተወሰደበት ነገር Eንዲመለስ ወይም በሰላማዊ ይዞታው ላይ የተነሣው ሁከት Eንዲወገድለት ክስ ለማቅረብ ይችላል። በተያዘው ጉዳይ ተጠሪዎች ቀድሞውኑ ከAመልካች ጋር የኪራይ ውል ፈጽመው በቤቱ ኪራይ Eየከፈሉ ረጅም ጊዜ ኖረዋል። በመሆኑም የቀድሞ ግንኙነቱ Eንዲቀጥል ተጠሪዎች የኪራይ ውል Eንዲፈርሙ መጠየቁ በተጠሪዎች ሰላማዊ ይዞታ ላይ ሁከት መፍጠር ነው Aያሰኝም።
በልላ በኩል ተጠሪዎች ለAመልካች የከፈሉት ገንዘብ Eንዲመለስላቸው ጠይቀዋል። ከመዝገቡ Eንደተመለከትነው ተጠሪዎች ይህንን ጥያቄ ያቀረቡት የቤቱ ባለሃብት ነን በማለት መሆኑን ለመገንዘብ ችለናል። ነገር ግን የማይንቀሣቀስ ንብረት ባለሃብት ለመሆን የቤቱ ባለቤትነት ምስክር ወረቀት መቅረብ Aለበት። ተጠሪዎች የቤቱ ባለሃብት ለመሆናቸው የባለቤትነት የምስክር ወረቀት Aላቀረቡም ወይም በቤቱ ላይ በስማቸው ከ15 ዓመት በላይ ግብር Eየከፈልን የቤቱ ባለሃብት ሆነናል በማለት ያቀረቡትም ክርክር የለም።
No topics extracted.
በመሆኑም ተጠሪዎች የቤቱ ባለሃብት ናቸው ለማለት የሚያስችል ሁኔታ Aላገኘንም፤ በዚህም ምክንያት ተጠሪዎች የቤቱ ባለቤት ስለሆኑ የከፈሉት የኪራይ ገንዘብ Eንዲመለስላቸው ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ሆኖ Aግኝተነዋል።
ው ሣ ኔ
የከተማ ነክ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ሰበር ችሎት በመ/ በሐምል 2A ቀን 1999 ዓ.ም የከተማ ነክ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት 215 216 በመ/ በታህሣሥ 24 ቀን 199A ዓ.ም. Eንዲሁም የA/A ከተማ የመ/ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ ግንቦት 3A ቀን 1997 ዓ.ም የሰጡዋቸው ውሣኔዎች ተሽረዋል።
ተጠሪዎች ያቀረቡት ክስ ተቀባይነት የለውም።
ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ይቻቻሉ።
የማይነበብ የAምስት ዳኞች ፊርማ Aለበት።