No summary available.
ሚያዝያ 28 ቀን 2AAA ዓ.ም ዳኞች፡- ዓብዱልቃድር መሐመድ ሐጎስ ወልዱ ታፈሰ ይርጋ መድሕን ኪሮስ ሡልጣን Aባተማም Aመልካች፡- ወ/ሮ የዝና ተስፋሁን ቀረበች ተጠሪ፡- መምህር ጥሩAየሁ Eውነቱ ቀረበ መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል።
በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር Aቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ በAመልካች Eና በተጠሪ መካከል ጋብቻ Aለ ወይስ የለም በሚል ጭብጥ ላይ ተመሥርቶ የተደረገውን ክርክር የሚመለከት ነው። ክርክሩ ሲጀመር ከሣሽ የነበረችው የAሁንዋ Aመልካች ስትሆን በተጠሪ ላይ ክስ የመሰረተችው ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በጋብቻ ተሳስረን ለ25 ዓመት ኖረናል፣ በዚህ ጊዜም Aምስት ልጆች ወልደናል፣ ተከሣሽ ግን በመካከላችን የተመሰረተውን የጋብቻ ግንኙነት Eንደልለ በመቁጠር ግድታውን ላወጣ ስላልቻል ፍ/ቤቱ ተከሣሽን Aስቀርቦ በመጠየቅ ተገቢው ውሣኔ ይሰጠኝ በማለት ነው። ተጠሪም በበኩሉ ለቀረበበት ክስ በሰጠው መልስ በAንድ በኩል ከAመልካች ጋር በAንድ ቤት ለ25 ዓመት ያክል Aብረው መኖራቸው Eና በዚህ ጊዜ ውስጥ Aምስት ልጆች 249 250 መውለዳቸውን ሲያምን፤ በልላ በኩል ደግሞ Aመልካች በሰራተኛነት የቀጠራት Eንጂ ሚስቱ Eንዳልሆነች፣ በመሃከላቸው የተመሰረተ ጋብቻም Eንደልለ በመግለጽ ክዶ ተከራክሯል። ከዚህ በኋላም ፍ/ቤቱ በሁለቱም በኩል የቀረበውን ክርክር Eና ማስረጃ ሰምቶ በAመልካች Eና በተጠሪ መካከል የተመሰረተ ጋብቻ የለም። ባልና ሚስት Aይደሉም በማለት ወስኗል። በዚህ ውሣኔ ላይ ይግባኝ የቀረበላቸው የበላይ ፍ/ቤቶችም ውሣኔውን Aጽንተዋል። የሰበር Aቤቱታው የቀረበው በዚሁ ላይ ነው።
Eኛም Aመልካች መስከረም 12 ቀን 2AAA ዓ.ም በፃፈችው ማመልከቻ ያቀረበችውን Aቤቱታ መሰረት በማድረግ ተጠሪን Aስቀርበን ክርክሩን ሰምተናል። Aቤቱታው በሰበር ችሎት Eንዲታይ የተወሰነው Aመልካች ከተጠሪ ጋር የነበራት ግንኙነት የባልና ሚስት ሁኔታ” Aያሣይም የመባሉንና Aመልካች በ2ኛ ደረጃ ያነሣችው ከጋበቻ ውጪ Aብሮ የመኖርን መነሻ ያደረገ ክርክርም Eንደዚሁ ውድቅ የመደረጉን Aግባብነት ለመመርመር ነው። በዚህ መሰረትም Eነዚህን ነጥቦች ከስር ጀምሮ ከተደረገው ክርክር፣ Aቤቱታ ከቀረበበት ውሣኔ Eና ከሕጉ ጋር Aገናዝበን መርምረናል።
ከሥር ጀምሮ የተደረገውን ክርክር Eና የተሰጡትን ውሣኔዎች በዝርዝር ተመልክተናል። Aመልካች በወረዳ ፍ/ቤት ክስ የመሰረተችው የተጠሪ ሚስት ነኝ፤ በመሃከላችን የጋብቻ ግንኙነት Aለ በማለት ቢሆንም፤ ሚስት Aይደለሽም በማለት ፍ/ቤቱ ከወሰነ በኋላ ከጋብቻ ውጪ Aብሮ መኖርን መሰረት ያደረገ የንብረት ክፍፍል ውሣኔ Eንዲሰጥላት ጭምር በመከራከር ዋነኛ ጉዳዩን በይግባኝ የሰሙት ፍ/ቤቶችም በዚህ ነጥብ ጭምር ውሣኔ መስጠታቸውን ለመገንዘብ ችለናል። ልላው ከተሰጡት ውሣኔዎች መገንዘብ የቻልነው ፍ/ቤቶቹ በAመልካች Eና በተጠሪ መካከል የጋብቻ ግንኙነት የለም ለማለት የቻሉት ክርክሩን ከቀረቡላቸው ማስረጃዎች ጋር Aገናዝበው ከመረመሩና ካመዛዘኑ በኋላ Eንደሆነ ነው።
በመሆኑም ፍ/ቤቶቹ በማስረጃ Aመዛዘን ረገድ ስህተት ፈጽመዋል ለማለት የምንችልበት ምክንያት ስለልለ ጋብቻን በሚመለከት Aመልካች ያቀረበችውን Aቤቱታ Aልተቀበልንም።
ጋብቻ Aለ ወይስ የለም የሚለውን ነጥብ በተመለከተ የቀረበውን ክርክር በዚህ ሁኔታ ካለፍን ቀጥለን የምንመለከተው ጋብቻ ሳይፈፀም Eንደባልና ሚስት Aብሮ መኖርን መሰረት በማድረግ የቀረበውን ክርክር ነው።
ከላይ Eንደተገለፀው Aመልካች Eና ተጠሪ በAንድ ቤት ለ25 (ሃያ Aምስት) ዓመት ያክል Aብረው ከመኖራቸውም በላይ፤ በዚህ ጊዜም Aምስት ልጆችን ወልደዋል። ተጠሪም ይህ” በፍሬ ነገር ረገድ የተረጋገጠውን ሃቅ የሚቀበል ቢሆንም፤ በልላ በኩል ግን ከAሰሪና ሰራተኛ ያለፈ ግንኙነት የለንም በማለት ተከራክሮAል። ይህም ሆኖ ግን Eሱ Eንደሚለው በሰራተኛነትም ደመወዝ Eየከፈላት ስለመቆየቱ Aላስረዳም፤ በዚህ መልክም Aልተከራከረም። ክርክሩን በይግባኝ ሰምቶ የመጨረሻ ውሣኔ የሰጠው የAማራ ብ/ክ/መ/ጠ/ፍ/ቤትም ሲሆን፣ Aመልካች የተጠሪ የቤት ሰራተኛ ናት ብሎ Aልደመደመም።
ውሣኔውን የሰጠው የAመልካች ምስክሮች ጋብቻ ስለመፈፀሙ Aላስረዱም፤
ከጋብቻ ውጪ Eንደባልና ሚስት ሆነው Aብረው ስለመኖራቸውም በማስረጃ Aልተረጋገጠም ማለት Eንደሆነ ከውሣኔው ለመገንዘብ ችለናል።
ክርክሩን በመጀመሪያ ደረጃ በሰማው በደብረማርቆስ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በAመልካች ተቆጥረው ከተሰሙት ምስክሮች Aንዱ የAመልካች Eና የተጠሪ ትልቁ ልጅ Eንደሆነና Eሱም በሰጠው ምስክርነት Aባትና Eናቱ ባልና ሚስት ናቸው ብሎ Eንደሚያምን ማስረዳቱን ከወረዳው ፍ/ቤት ውሣኔ ተመልክተናል። Eንደምንመለከተው ተጠሪ Aመልካችን ከሃያ Aምስት ዓመት በፊት በቤት ሰራተኛነት ቀጥሬያታለሁ ቢልም፤ ለሃያ Aምስት ዓመት ያክል Aብረው የኖሩት ግን Eሱ ከሚለው በEጅጉ በተለየ ሁኔታ ነው። Aብረው ለብዙ ዓመታት መኖራቸው ብቻ ሣይሆን Aምስት ልጆች ወልደው በጋራ ሲያሣድጉም የመቆየታቸው ሁኔታ ሲታይ በጋብቻ ተሣስረው ከሚኖሩት ወንድና ሴት ተለይተው የሚታዩ Aይመስሉም። ትልቁ ልጃቸው Eንደባልና ሚስት Aድርጎ የሚያያቸው መሆኑን ለፍ/ቤቱ ያስረዳውም ከዚህ በመነሣት Eንደሆነ መገመቱ የሚያስቸግር Aይደለም። በበኩላችን Eንደምናየው የAመልካች Eና የተጠሪ Aብሮ የመኖር ሁኔታ በፍድራሉ መንግሥት የቤተሰብ ሕግም ሆነ በAማራ ብ/ክ/መ/ የቤተሰብ ሕግ ከጋብቻ ውጪ Eንደባልና ሚስት Aብኖ መኖርን በተመለከተ የተቀመጡትን መስፈርቶች በሚገባ የሚያሟላ ነው። ሲጠቃለል በAመልካች Eና በተጠሪ መካከል የጋብቻ ግንኙነት Aለ ለማለት ባይቻለም፤
No topics extracted.
ከጋብቻ ውጪ Eንደባልና ሚስት በመሆን Aብረው መኖራቸው ግን የሚያጠራጥር Aይደለም። በመሆኑም ከጋብቻ ውጪ Eንደባልና ሚስት Aብሮ መኖርን የሚያሣይ ሁኔታ በሚል በስር ፍ/ቤት የሰጠው ውሣኔ ትክክል Aይደለም። ውሣኔው መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው ለማለት ችለናል።
ው ሣ ኔ
A9277