No summary available.
ሰኔ 26 ቀን 1999 ዓ.ም ዳኞች፡- መንበረፀሐይ ታደሰ ዓብዱልቃድር መሐመድ Aሰግድ ጋሻው ሒሩት መለሰ ተሻገር ገ/ሥላሴ Aመልካች፡- ወ/ሮ Aንማው ዘገየ መልስ ሰጭ፡- ወ/ሮ ወርቄ መኰንን መዝገቡን መርምረን ፍርድ ሰጥተናል።
በዚህ መዝገብ የቀረበው ክርክር ከሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች ሚስት ማን ነች? የሚለውን የሚመለከት ነው።
ክስ የቀረበለት የከፍተኛው ፍ/ቤት በዚህ ነጥብ ላይ ግራ ቀኙ ያቀረቡትን ክርክርና ማስረጃ ተመልክቶ የAሁን መልስ ሰጭ ከሟች ጋር በ1983 ዓ.ም ጋብቻ የፈፀመች ቢሆንም በኑሮ Aለመግባባት በEርሷ ክስ Aቅራቢነት በወረዳው ፍ/ቤት በ1992 ዓ.ም ጋብቻው Eንዲፈርስ ተደርጓል።
ይህንንም Eርሷ Aልካደችውም። በEርሷ በኩል የቀረበው ክርክር Eንደገና በመስከረም A8 ቀን 1995 ዓ.ም ታርቄያለሁ የሚል ነው። ይሁን Eንጂ ለማህበራዊ ዋስትና መ/ቤት የቀረበውን ማስረጃ Eንደተመለከትነው በወረዳው ፍ/ቤት በተሰጠው የፍቺ ውሣኔ መሰረት ሟች ከAሁን መልስ ሰጭ ለተወለዱት ልጆች Eስከ 1996 ዓ.ም ድረስ የልጅ ቀለብ በወር 50.00 ሲከፍል የቆየ መሆኑን ነው። መልስ ሰጭ Eንደምትለው በ1995 ዓ.ም ታርቃ ቢሆን ኖሮ ሟች ለልጆች ቀለብ ባልከፈለ ነበረ። ይህም የሚያመለክተው መስከረም A8 ቀን 1995 ዓ.ም ታርቄያለሁ ስትል ያቀረበችው ማስረጃ Eምነት የሚጣልበት Aለመሆኑን ነው በማለት መልስ ሰጭ የሟች ሚስት Aይደለችም፤ በተቃራኒው 184 185 የAሁን Aመልካች የሟች ሚስት መሆኗን በበቂ ማስረጃ Aስደግፋ ያስረዳች ስለሆነ ሚስት ናት በማለት ወስኗል።
የይግባኝ Aቤቱታ የቀረበለት የክልሉ ጠ/ፍ/ቤትም የይግባኝ ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ የAሁን Aመልካች በደምበጫ ወረዳ ፍ/ቤት መልስ ሰጭ ደግሞ በደ/ማርቆስ ወረዳ ፍ/ቤት ሚስትነታቸውን Aረጋግጠው Aስወስነዋል።
ሚስትነት ተረጋግጦ የተሰጠውን ውሣኔ Aንዳቸው የAንዳቸውን Aላሻሩትም፤
ውሣኔው ሕጋዊ ውጤት ያለው ነው። ስለሆነም ሁለቱም ሚስቶች ናቸው በማለት ከመብት በኋላ የጡረታ Aበሉ ለማን ይገባል የሚለውን በሚመለከት Aበል በየጊዜው ለመክፈል ከደመወዝ ተቀናሽ Eየሆነ ከተጠራቀመው የሚከፈል Eስከሆነ ድረስ ከሟች ጋር ረዘም ላለ ጊዜ Aብራ ለቆየችው መሆን ይገበዋል።
በዚህ ጉዳይ መልስ ሰጭ ለ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከሟች ጋር በትዳር የቆየች በመሆኑ የጡረታ Aበሉ ለመልስ ሰጭ ይክፈል ከሚለው መደምደሚያ ደርሷል።
የሰበር Aቤቱታ የቀረበውም የሥ/ፍ/ቤት የጡረታ Aበሉ ለመልስ ሰጭ ላከፈል ይገባል ለሚለው ውሣኔው መሰረት ያደረገው ምክንያት ሕጋዊ መሰረት የለውም፤ Eንዲሁም የከፍተኛው ፍ/ቤት የግራ ቀኛችን ክርክርና ማስረጃ መርምሮ የAመልካችን ሚስትነት ለይቶ በAግባቡ ወስኖ Eያለ የጠ/ፍ/ቤት ሁለታችንንም ሚስቶች ናቸው በማለት መወሰኑ Aግባብ Aይደለም የሚል ነው።
መልስ ሰጭም ውሣኔው ላፀና ይገባል የምትልበትን ምክንያት በመግለጽ ተከራክራለች።
Eኛም ጉዳዩን ተመልክተናል Eንደተመለከትነውም ሁለቱም ወገኖች በየፊናቸው የሟች ሚስት Eና የልጆቻቸው ሞግዚት መሆናቸውን በተለያዩ ፍ/ቤት Aረጋግጠው Aስወስነዋል። ይህ ውሣኔ በይግባኝ Aማካኝነት የተሻረ ለመሆኑ በግራ ቀኙ በኩል የቀረበ መከራከሪያ የለም። ይህም ሲሆን ሚስትነትን በማረጋገጥ የተሰጠው ውሣኔ ሕልውና ያለው Eና ሕጋዊ ውጤትን የሚያስከትል ነው። የጠ/ፍ/ቤቱ ይህንኑ መሰረት Aድርጎ ሁለቱም ወገኖች Aመልካችና መልስ ሰጭ የሟች ሕጋዊ ሚስቶች ናቸው ሲል የሰጠው ውሣኔ በAግባቡ ሆኖ Aግኝተነዋል።
ይሁን Eንጂ የጠቅላይ ፍ/ቤት በዚህ ውሣኔ መገደብ ሲገባው ከዚህ Aልፎ የጡረታ Aበሉ ለየትኛዋ ሚስት ይገባል የሚለውን ጭብጥ ይዞ Eና ይህንንም ለመለየት ከሟች ጋር ለረዥም ጊዜ በትዳር የኖረችው የትኛዋ ናት የሚለውን መሰረት Aድርጎ የጡረታ Aበሉ ለAሁን መልስ ሰጭ ላከፈል ይገባል ሲል መወሰኑ በዚያው ጉዳይ ሁለቱም የሟች ሚስቶች ናቸው በሚል ከሰጠው ውሣኔ ጋር የሚጠርስ ሆኖ Aግኝተነዋል። Eንደቀረበለት ጥያቄ ሚስትነት በማረጋገጥ ረገድ ዳኝነት መስጠት ሲገባው ከተጠየቀው ዳኝነት ውጭ በመሄድና ¾T>eƒ’ƒ” ውሣኔ ውጤት በሚያስቀር Aኳኋን መወሰኑ ሥነ ሥርዓታዊ የሕግ ስህተት ፈጽሟል።
ው ሣ ኔ
ወ/ሮ Aንማው ዘገዬ Eና ወ/ር ወርቄ መኰንን ሁለቱም የሟች ሚስቶች ናቸው፤ የጡረታ Aበሉም ለሁለቱም ላከፈል ይገባል ብለናል።
የA/ብ/A/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት በፍ/ብ/ይ/መ/ቁ. A7542 በየካቲት 16 ቀን 1998 ዓ.ም የሰጠውን ውሣኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 348(1) መሰረት ተሻሽሐል።
No topics extracted.
የምሥ/ጎጃ/መስ/ዞን ከፍተኛው ፍ/ቤት በመ/ቁ. 1A39 በመስከረም 20 ቀን 1998 ዓ.ም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል።