No summary available.
ሐምል 13 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም.
ዳኞች፡- ሐጏስ ወልደ አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ ነጋ ደፍሳ አዲነ ንጉሴ አመልካች፡- ሕብረት ባንክ /አ.ማ/ - ነገረ ፈጅ ንጉሴ ኪዲኔ ቀረቡ።
ተጠሪ፡- አቶ ዓሉ አብደ - ጠበቃ አቶ ደምሴ ልዐልሰገድ ቀረቡ።
መዝገቡን መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል።
ጉዲዩ የቀረበው አመልካች የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የሰጠው ውሣኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዱታረምልኝ በማለት ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው። ክርክሩ የተጀመረው በሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው። በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተጠሪ ላይ በፍርድ የተወሰነላቸው ገንዘብ እንዲለ በመግለፅ ወሐቢይ መሐመድ የአፈፃፀም ክስ አቅርበዋል። በአፈፃፀሙ ንብረትነቱ የተጠሪ የሆነ የሰሉጥ ማበጠሪያ ማሽን ድርጅት መጋዘን የተያዘ በመሆኑ አመልካች በክርክሩ ጣልቃ ገብቶ በሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅቱ መጋዘን የብድር መያዣ በመሆኑ የቀዲሚነት መብት አለኝ። ላልች የፍርድ ባለመብቶች የሰሉጥ ድርጅቱ ሲሸጥ ከእኔ የተረፈ ገንዘብ ከተገኘ በተረፈው ላይ ብቻ ነው ፍርድ የማስፈፀም መብት ያላቸው የሚል ጥያቄ አቅርቧል። የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአመልካችን ጥያቄ ተቀብል የሀራጅ ማስታወቂያው በሬድዮና በቴሉቪዥን እንዱነገር ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ የሀራጅ ማስታወቂያው ሳይነገር የቀረ መሆኑ የሥር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ያሳያል። ከዚህ በኋላ አመልካች በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት በመያዣነት የያዘውን የሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅት መጋዘን ሸጦ ቀሪ ገንዘብ ከተገኘ ለላልች የፍርድ ባለመብቶች ለማከፊፈል እንዱችል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዱሰጥለትና መያዣውን በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሐራጅ ለመሸጥ የተጀመረው አፈፃፀም እንዱቆም ጥያቄ አቅርቧል። የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአመልካችን ጥያቄ በመቀበል አመልካች በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት መያዣውን እንዱሸጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል። በዚህ ውሣኔ ቅር በመሰኘት ተጠሪ ይግባኝ ለክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርበዋል። የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ አመልካች በመያዣ የያዘውን የሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅት መጋዘን እንዱሸጥ እድል ተሰጥቶት ጨረታ ማስታወቂያ ካወጣ በኋላ የተወው በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 97/90 መያዣውን በራሱ የመሸጥ መብቱን ትቷል። ስለሆነም የሐራጅ ሥርዓቱ መከናወን ያለበት አፈፃፀሙን በጀመረው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል እንጂ በአመልካች በኩል መሆን የለበትም በማለት ወስኗል።
አመልካች የካቲት 15 ቀን 2003 ዓ.ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት አመልካች መያዣውን የመሸጥ መብቱን ከፈቃደ ለቋል በሚል የተሳሳተ የሕግ ትርጉም በመስጠት በአዋጅ ቁጥር 97/90 መያዣውን በመሸጥ ብድራችንን የመሰብሰብ መብታችንን የሚያሳጣ ውሣኔ ወስኗል። ይኸም መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዱታረምልኝ በማለት አመልክቷል። ተጠሪ በበኩላቸው ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም በተፃፈ መልስ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅቱን ለመሸጥ የመጀመሪያ ሐራጅ እንዱወጣ ካደረገ በኋላ አመልካች መያዣውን በአዋጅ ቁጥር 97/90 እንዱሸጥ በማለት የሰጠውን ትዕዛዝ የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሻረው ባግባቡ ነው መሰረታዊ የሕግ ስህተት የለበትም በማለት ተከራክረዋል፤ አመልካች የመልስ መልስ አቅርበዋል።
ከሥር የክርክሩ አመጣጥና በሰበር ያቀረበው ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አመልካች መያዣውን የመሸጥ መብቱን በፍላጎቱ ትቶቷል። ሁለተኛ መያዣውን በአዋጅ ቁጥር 97/90 መሰረት ለመሸጥ ያቀረበው ጥያቄ ተገቢነት የለውም በማለት የሰጠው ውሣኔ በአግባቡ ነው? ወይስ አይደለም? የሚለውን ጭብጥ በመያዝ ጉዲዩን መርምረናል።
ጉዲዩን እንደመረመርነው አመልካች የፍርድ ባለዕዲ የሆኑትን የተጠሪ ሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅት መጋዘኖች በመያዣነት የያዘ መሆኑ አመልካችና ተጠሪ የሚካካደበት ነጥብ አይደለም።
የመንግስትም ሆኑ የግል ባንኮች ለአበደሩት ብድር ዋስትና እንዱሆን የያዙትን የማይንቀሳቀስ ንብረት የፍትሐብሕር ሥነ ሥርዓት ሕግ ድንጋጌዎችን መሰረት በማድረግ በሐራጅ በመሸጥ ለአበደሩት ብድር መክፈያነት ሉያውለ የሚችለበት ሥልጣንና ኃላፉነት በአዋጅ ቁጥር 97/90 በሕግ አውጭው ተሰጥቷቸዋል። ሕግ አውጭው በአገሪቱ የሚገኙ ባንኮች በውል የያዙትን የመያዣ ንብረት ራሳቸው በሐራጅ ሸጠው ዕዲቸውን ለመሰብሰብ የሚያስችላቸው ሥልጣን የሰጠበት ዋነኛው ምክንያት የገንዘብ ተቋማቱ መያዣውን በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በማሸጥ ያበደሩትን ገንዘብ ለማስመለስ በሚጥሩበት ጊዜ የተለያዩ ችግሮች ስለሚያጋጥሟቸውና በዚህ ምክንያት ዕዲቸውን ለመሰብሰብና መያዣውን በወቅቱና በዋጋቸው ለመሸጥ የማይችለ በመሆናቸው መሆኑን በአዋጅ ቁጥር 97/90 መግቢያ ላይ በግልፅ አስቀምጧል። ሕግ አውጭው የገንዘብ ተቋማቱ በመያዣ የያዙትን ንብረት በሐራጅ ሲሸጡ በፍትሐብሕር ሥነሥርዓት ሕግ ከአንቀፅ 394 እስከ አንቀፅ 449 ያለትን ድንጋጌዎች እንደ አግባብነታቸው የመከተል ኃላፉነት ያለባቸው መሆኑን በአዋጁ አንቀፅ 6 ከመደንገጉም በላይ በሽያጭ ሂደቱ ሕግን በመተላለፍ ሸያጩን ቢፈፅም ባንኩ በባለ ዕዲው ላይ ለሚያደርሰው ጉዲት ተጠያቂነት ያለበት መሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 7 በግልፅ ተደንግጓል።
ስለሆነም አመልካች በመያዣነት የያዘውን የተጠሪ ሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጀት መጋዘን በራሱ በሐራጅ የመሸጥና ዕዲውን የመሰብሰብ መብት ያለው መሆኑ በአዋጅ ቁጥር 97/90 አንቀፅ 3 በግልፅ ተደንግጓል። አመልካች ይህንን በሕግ የተሰጠውን ሥልጣን ለመጠቀም የፍርድ ቤት ውሣኔም ሆነ ፈቃድ አያስፈልገውም። አመልካች ከዚህ በፉት መያዣውን የመሸጥ መብቱን በፈቃደ ትቶታል የሚለው የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክንያት ሕግ አውጭው ከጅምሩ አዋጅ ቁጥር 97/90 በማወጅ ባንኮች መያዣቸውን ለመሸጥ የሚያስችላቸውን ሥልጣንና ኃላፉነት የሰጠበትን መሰረታዊ ዓላማ ያላገናዘበና የሕግ መሰረት የላለው በመሆኑ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም። ስለሆነም የክልለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት አመልካች በመያዣነት የያዘውን የተጠሪን የሰሉጥ ማበጠሪያ ድርጅት መጋዘን በአዋጅ ቁጥር 97/90 ራሱ መሸጥ አይችልም። የሐራጅ ሽያጩ በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በኩል ይፈፀም በማለት የሰጠው ውሣኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው በማለት ወስነናል።
ው ሣ ኔ
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል።
የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሣኔ ፀንቷል።
በዚህ ፍርድ ቤት የወጣውን ወጪና ኪሣራ ግራ ቀኙ ለየራሳቸው ይቻለ። መዝገቡ ይመለስ።
No topics extracted.