No summary available.
ግንቦት 29 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም ዳኞች፡- ተገኔ ጌታነህ ሐጏስ ወልደ አልማው ወላ ነጋ ደፍሣ አዲነ ንጉሴ አመልካች፡- ወ/ሮ ፊጡማ ጀማል - ቀረቡ ተጠሪ፡- ወ/ሮ ፊጡማ ኡስማን ከጠበቃ መሐመድ ሀሰን ጋር - ቀረቡ **
መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል።
**
ጉዲዩ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 መሰረት የሚስተናገደውን ጥያቄ የሚመለከት ነው።
ክርክሩ የተጀመረው በፋዳራል ከፍተኛ ሸሪዓ ፍ/ቤት ሲሆን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 መሰረት አቤቱታውን ያቀረቡት የአሁኑ አመልካች ናቸው። የአመልካች የአቤቱታ ይዘትም ባጭሩ፡አመልካች በከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በነበረው የይግባኝ ክርክር የክርክሩ ተካፊይ መሆን ሲገባቸው ሣይከራከሩበት በቀድሞ አወቃቀር በወረዲ ዐ8 ፣ ቀበላ ዐ2 ክልል ወስጥ በሚገኝና ቁጥሩ 1ዐ2 በሆነው የግል የመኖሪያ ቤታቸው ላይ በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የተሰጠው ውሣኔ መብታቸውን የሚጏዲ ከመሆኑም በላይ በተከሰሱበት ጉዲይ የመከላከል ህገ መንግስታዊ መብታቸውን የሚጋፊ በመሆኑ አመልካች በላለበት የተሰጠው ውሣኔ ተነስቶ የክርክሩ ተካፊይ እንዱሆኑ ይደረግላቸው ዘንድ ዲኝነት መጠየቃቸውን የሚያሣይ ነው። አቤቱታው ጋርም ከውጭ አገር የነበሩ መሆኑን የሚያሣዩ የሰነድ ማስረጃዎችን አያይዘው አቅርበዋል፡ አቤቱታው የቀረበለት ከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤትም አመልካች አቤቱታውን ያቀረቡት ጉዲዩ ውሣኔ ካገኘ ከስድስት ዓመት በሁዋላ ከመሆኑም በላይ ጉዲዩ የቤተሰብ እንደመሆኑ መጠን አልሰሙም ነበር ለማለትም የሚቻል አይደለም በሚል ምክንያት የአመልካች አቤቱታን ውድቅ አድርጏ ብይን ሰጥቷል። በዚህ ብይን አመልካች ባለመስማማት ይግባኛቸው ለፋዳራለ ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አቅርበው ግራ ቀኙ ከተከራከሩ በሁዋላ በከፍተኛው ሸሪዓ ፍርድ ቤት በነበረው የይግባኝ ክርክር አመልካች በወኪላቸዉ አማካኝነት የክርክሩ ተካፊይ የነበሩ መሆኑ መረጋገጡን ጉዲዩ የቤተሰብ ከመሆኑም በላይ አመልካች ይኖሩበት ከነበረው ውጪ አገር ወደ ኢትዮጽያ ሲመላለሱ የነበረ መሆኑ መረጋገጡን በምክንያትነት በመያዝ በይግባኙ ክርክር ውሣኔ ከተሰጠ ከስድስት ዓመት በሁዋላ ጉዲዩ ባለሁበት ይታይልኝ ተብል የቀረበው የአመልካች ጥያቄ በህጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ያልቀረበና በበቂና ህጋዊ ምክንያት ያልተደገፈ ነው በማለት የከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤትን ብይን አጽንቶታል። የአሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበውም ይህኑን ውሣኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው። የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘት ሲታይም የክርክሩ ተካፊይ ሣይሆኑ በግል ገንዘባቸው በገዙት ቤት ላይ ተገቢ ያልሆነ ውሣኔ ማረፊን ገልጸው የበታች ፍርድ ቤቶች ጉዲዩ ባለበት እንዱታይላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ ማድረጋቸው ህጋዊ አለመሆኑን በመዘርዘር ውሣኔው እንዱሻር ዲኝነት መጠየቃቸውን የሚያሣይ ነው። አቤቱታው ተመርምሮም የአመልካች አቤቱታ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 መሰረት ላታይ የሚችልበት አግባብ መኖር ያለመኖሩን ሣያረጋግጡ አመልካች በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 መሰረት ወደ ክርክሩ ለመግባት በቂ ምክንያት የላትም የመባለን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ለሰበር ችልቱ እንዱቀርብ ተደርጏአል። በዚህም መሰረት ለተጠሪ ጥሪ ተደርጏላቸው ቀርበው ግራ ቀኙ በጽሁፍ ክርክር አድርገዋል። ከላይ የተመለከተው የክርክሩ አመጣጥ ሲሆን ይህ ችልትም የግራ ቀኙን ክርክር አቤቱታው ከቀረበበት ውሣኔና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች እንዱሁም ከፋዳራል ከፍተኛ ሸሪዓ ፍ/ቤት ካስቀረብነው የመ/ቁጥር 51/93 እና 4640/2001 ፣ ከፋዳራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ካስቀረብነው መ/ቁጥር 68/2002 ጋር አዛምደን በሚከተለው መልኩ መርምረናል። እንደመረመርነውም ተጠሪ በላለበት የተሰጠው ውሣኔ ሉነሣ ይገባል? ወይስ አይገባም? የሚለውን ጭብጥ መመልከቱ ተገቢ ሁኖ አግኝተነዋል።
የፍታብሓር ክርክሮች የሚመሩት በ1958 ቱ የፍትሐብሕር ሥነ ሥርዓት ህግ መሰረት ነው። የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች የክርክር አመራር ስርዓትም በዚህ የፍታብሓር ሥነ ሥርዓት ህግ ስለመሆኑ የአዋጅ ቁጥር 188/92 አንቀጽ 6/1/ ድንጋጌ በግልጽ ያሣያል። የፍታብሓር ሥነ ሥርዓት ህግ አካቶ ከያዛቸው ጉዲዮች ውስጥ አንደ የተከራካሪ ወገኖች በክርክሩ ወቅት ያለመቅረብና ውጤቱ ነው። በዚህም መሰረት መጥሪያ ተልኮለት በተገቢው መንገድ የደረሰው መሆኑ በተረጋገጠበት ተከሣሽ /መልስ ሰጪ/ ላይ ፍ/ቤቱ ሉከተለው የሚገባው ሥርዓት ጉዲዩ ተከሣሹ/መልስ ሰጪ በላለበት የሚሰማበት ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 70/ሀ/ ስር ተመልክቷል።
ላላው በሥነ ሥርዓት ህጉ የተመለከተው ሥርዓት ተከሳሹ ሉከተለው የሚገባው መፍትሓ ነው።
ክርክሩ በላለበት እንዱቀጥል የተደረገበት ተከሣሽ በተከታዩ ቀነ ቀጠሮ ቀርቦ በቂ ሆኖ በሚገመት እክል ምክንያት በመጀመሪያ ቀነ ቀጠሮ ያለመቅረቡን ካስረዲ መከላከያውን አቅርቦ የመከራከር መብት ያለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 72 ያስገነዝባል። እንዱሁም የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.
78/1/ አንድ ተከሣሽ /መልስ ሰጪ/ በክርክሩ ላይ ቀርቦ መልስ ሣይሰጥ ወይም ተገቢውን መከራከሪያ ሣያቀርብ በመቅረቱ በላለበት አንድ ውሣኔ ወይም ትዕዛዝ የተሰጠ ከሆነ ውሣኔው ወይም ትዕዛዙ መሰጠቱን በተረዲው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ቀርቦ ትዕዛዙ ወይም ውሣኔው እንዱነሣለት የማመልከት መብት እንዲለው ተደግንጓል። አቤቱታ አቅራቢ በዚህ መሰረት ማመልከቻ በሚያቀርብበት ጊዜ የጥሪው ትዕዛዝ በሚገባ ያልደረሰው መሆኑን ወይም ክርክሩ ሉሰማ በተቀጠረበት ቀን ቀርቦ መከራከሪያውን ያላሰማው ወይም መልስ ያልሰጠው በበቂ ምክንያት መሆኑን ፍርድ ቤቱ የተረዲ እንደሆነ የተከሣሹ /የመልስ ሰጪ/ አቤቱታ ላንደኛው ወገን ተከራካሪ እንዱደርሰው ካደረገና ተገቢውን ኪሣራ ወይም መቀጮ እንዱከፍል ካዘዘ በኋላ ትዕዛዙን ወይም ብይኑን በማንሣት ክርክሩን እንደገና መስማት እንዲለበት የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78/2/ ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ ያሣያል።
ወደተያዘው ጉዲይ ስንመለስ አመልካች በላለሁበት በግል ንብረቴ ላይ ውሣኔ ተሰጥቶብኛል የሚለት ጥር ዐ9 ቀን 1995 ዓ.ም ሲሆን ይኸው ውሣኔ ተነስቶ ወደ ክርክሩ ልገባ ይገባል በማለት አቤቱታ ያቀረቡት ደግሞ ነሐሴ 19 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም ነው። ከላይ ከተጠቀሱት የስር ፍርድ ቤቶች መዛግብት መገንዘብ የተቻለው ደግሞ የአሁኗ አመልካች ወ/ሮ ኑሪያ ኡስማን /የሟች ሚስት/ እና ላልች አምስት የሚሆኑ የሟች ጀማል ሐምዛ የመጀመሪያ ደረጃ ወራሾች መሆናቸውን ገልጸው በሸሪዓ ህግ መሰረት የውርስ ንብረቱን ለመከፊፈል ንብረቱን ይዘዋል፣ የሟች ሁለተኛ ሚስት ናቸው ባሎቸው የአሁኗ ተጠሪ ላይ ክስ መስርተው የስር ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ተገቢ ነው ያለውን ውሣኔ ከሰጠ በሁዋላ ተጠሪ የአሁን አመልካች በግል የገዛሁት ንብረቴ ነው በሚለት ቤት ላይ የተሰጠውን የውሣኔ ክፍል በመቃወም ይግባኛቸውን ለፋዳራለ ከፍተኛ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አቅርበው የስር ከሣሾች የነበሩት፤ የአሁኗ አመልካች ጭምር በወ/ሪት ቀመሪያ ጀማል አማካኝነት ተወክለው የይግባኝ ክርክሩ ተካሂድ አከራካሪው ንብረት ላይ ተገቢ ነው የተባለ ውሣኔ የተሰጠበት መሆኑን ነው። አመልካች ራሣቸው የክርክሩ ተካፊይ ባይሆኑም በህጉ አግባብ የወከሎቸው እህታቸዉ ወ/ሪት ቀመሪያ ጀማል የክርክሩ ተካፊይ የነበሩ መሆኑን ከላይ የተጠቀሱት መዛግብት በሚገባ ያረጋግጣለ። ይህም የሚያሣየው አመልካች በህጉ አግባብ የክርክሩ ተካፊይ የነበሩ መሆኑን ነው። እንዱህ ከሆነ አንድ ሰው በውሣኔው ላይ የሚኖረውን ቅሬታ በይግባኝ ወይም በሰበር ስርዓት ማሣረም እንጂ ጉዲዩ በላለሁበት ታይቷል። ባለሁበት ላታይልኝ ይገባል በማለት አቤቱታ የሚያቀርብበት አግባብ የላለ መሆኑን ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 ድንጋጌ ይዘት የምንገነዘበው ጉዲይ ነው። ጉዲዩ ለሰበር ሰሚ ችልት ሲቀርብ የተያዘው ጭብጥ ሲታይም አከራካሪው ንብረት የክርክሩ ምክንያት የነበረ መሆኑንና አመልካችም በህጉ አግባብ ተወክለው የነበሩ ስለመሆኑ የክርክሩ ሂደት የሚያሣይ በመሆኑ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 358 መሰረት የአመልካች አቤቱታ ሉስተናገድ ይገባ ነበር ሉባይ የሚችል ባለመሆኑ ተገቢነት ያለው ሆኖ አላገኘነውም። በአጠቃላይ አመልካች በላለሁበት የተሰጠው ውሣኔ ይነሣልኝ በማለት ያቀረቡት አቤቱታ በሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ውድቅ መደረጉ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 ስር የተመለከተውን መመዘኛ መሰረት ያደረገ ሲሆን አመልካች የግል ቤቴ ላይ ተገቢ ያልሆነ ውሣኔ ተሰጥቷል በማለት የሚያቀርቡት ክርክር ደግሞ በይዘቱ በዋና ጉዲይ ላይ የቀረበ በመሆኑ የክርክሩን አመራር ስርዓት ካልሆነ በስተቀር የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች በስረ ነገር ስልጣናቸው ስር የሆኑ ጉዲዮች የሚቀርብላቸዉን አቤቱታና ክርክር የሚወስኑት የሸሪዓ ህግን መሰረት በማድረግ እንደሆነ በአዋጅ ቁጥር 188/92 በአንቀጽ 6/1/ በግልጽ የተደነገገ በመሆኑ አንድ ሰው ለሸሪዓ ፍርድ ቤት ክስ ወይም አቤቱታ ሲያቀርብና ተገቢ የተባለ ውሣኔ ከተሰጠ ሥነ ሥርዓታዊ ከሆነው ጭብጥና ጥያቄ ውጭ የሆኑት ጉዲዮች ለዚህ ሰበር ችልት ለማቅረብ የሚቻልበት አግባብ የላለ በመሆኑ ተቀባይነት ሉሰጠው የሚገባ ሁኖ አላገኘንም። በዚህም መሰረት በጉዲዩ ላይ በተሰጠው ውሣኔ መሰረታዊ የሆነ የሥነ ሥርዓት ህግ ስህተት የላለበት በመሆኑ ተከታዩን ወስነናል።
ው ሣ ኔ
በፋዳራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት በመ/ቁጥር 68/2002 ሐምል 28 ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም የተሰጠው ውሣኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 348/1/ መሰረት ጸንቷል።
አንድ ተከራካሪ ወገን በህጉ አግባብ በተወከለው ሰው የክርክሩ ተካፊይ መሆኑ ከተረጋገጠ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 78 መሰረት በላለሁበት የተሰጠ ውሣኔ ሉነሣልኝ ይገባል ለማለት አይችልም ብለናል።
በዚህ ችልት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሣራ የየራሣቸውን ይቻለ ብለናል።
በዚህ ችልት ጥር 19 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም ተሰጥቶ የነበረው እግድ ተነስቷል፤
ለሚመለከታቸው አካላት ይጻፍ። መዝገቡ ተዘግቷል፤ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ።
No topics extracted.