No summary available.
የሰ/መ/ቁ. 48ዐ12 ጥቅምት 3 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም ዳኞች፡- ተገኔ ጌታነህ ሐጎስ ወልደ ብርሃኑ አመነው አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ አመልካች፡- አቶ ዐመር ከድር ቀረቡ ተጠሪዎች፡- 1/ አቶ በዲዲ ሰቦቃ 2/ ወ/ሮ አበበች ተካ ጠ/ሰለሞን ሀብቴ ቀረቡ **
መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል።
**
በዚህ መዝገብ የቀረበው ክርክር የቤት ሽያጭ ውልን መነሻ ያደረገ ነው። አመልካች ተጠሪዎች ጅምር ቤት ከ1ዐ57 ካ.ሜ. ይዞታ ጋር ሸጠውለት ሳለ ክ/ከተማው ቦታውን ለልማት የወሰደ መሆኑን ጠቅሶ ሽያጭ የተፈፀመው የሻጮች ይዞታ ባልሆነ ቦታ ላይ ነው ሲለ ሽያጩ ዋጋ የለውም ተብል ወደነበሩበት እንዱመለሱ እንዱወሰን ዲኝነት ጠይቋል። ተጠሪዎች የይርጋ ክርክር በማቅረባቸው የፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የሽያጭ ውል ከተፈፀመ ከሁለት ዓመት በላይ ይሆናል በማለት የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ/2/ እና የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሥ/ሕግ 244/2/ሰ እና 245 በመመረኮዝ መዝገቡን ዘግቷል።
የፋዳራል ከፍተኛ ፍ/ቤትም ግራ ቀኙን ካከራከረ በኋላ ይህንኑ ብይን አጽንቷል።
የአመልካች ጠበቃ ለዚህ ሰበር ችልት ባቀረቡት አቤቱታ ውለ በሕጉ አላግባብ ያልተፈፀመ ስለመሆኑ እና ተጠሪዎች መብት የላላቸውን ቦታ የሸጡላቸው መሆኑን ዘርዝረው የሥር ፍ/ቤት ለጉዲዩ አወሳሰን ትክክለኛ ጭብጥ ሣይዝ የሰጠው ብይን እንዱታረም አመልክቷዋል።
ሰበር ችልቱም አቤቱታውን መርምሮ በዚህ ጉዲይ የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ/2/ ተፈፃሚነትን አስመልክቶ ለመመርመር ሲል ተጠሪዎች መልስ እንዱሰጡ አዝዟል።
የተጠሪዎች ጠበቃ በ14/5/2ዐዐ2 ዓ.ም ጽፍ ባቀረቡት መልስ የአመልካች ክስ ውል ማሰረዝ ይሁን ማፍረስ ግልጽነት የሚጎድለው ስለመሆኑ ጠቅሰው ተጠሪዎች ያደረጉት የሸያጭ ውል ዋጋ የለውም እንዱባልና ወደነበርንበት እንመለስ የሚለውም ውለ ከተደረገ ከ9 ዓመት በኋላ የቀረበ በመሆኑ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ በይርጋ ቀሪ መደረጉ በአግባቡ ነው በማለት የሥር ፍ/ቤት ውሣኔ እንዱፀና ጠይቀዋል።
የጉዲዩ አመጣጥ እና የግራ ቀኙ ክርክር ከፍ ሲል የተመለከተው ሆኖ እኛም ከተያዘው ጭብጥ አንፃር ከሕጉ አገናዝበን መርምረናል።
ከመዝገቡ መረዲት የተቻለው በግራ ቀኙ መካከል ነሐሴ 12 ቀን 199ዐ ዓ.ም በተደረገ ውል ተጠሪዎች ጅምር ቤት ለአመልካች መሸጣቸው እና በዚሁ አግባብም በግራ ቀኙ መካከል በውለ መሰረት የተፈፀመ ስለመሆኑ ነው።
አመልካች ውለ ዋጋ የለውም ተብል ግራ ቀኙ ከውለ በፉት ወደነበሩበት እንዱመለሱ እንዱወስን ዲኝነት የጠየቀው ለአመልካች የተሸጠው ይዞታ የሻጮች አልነበረም በሚል መነሻ ስለመሆኑም የሥር መዝገብ ያስረዲል። ከዚህ መረዲት የሚቻለው የውለ ጉዲይ ሕጋዊነት አከራካሪ ሆኖ የቀረበ መሆኑን ነው። በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1711 በግልጽ እንደተደነገገው የውለታው ጉዲይ /Object of the Contract/ የመወሰን መብት የተዋዋዮች ቢሆንም በሕግ የተወሰኑ ወይም የተከለከለ ጉዲዮች የተጠበቁ መሆናቸውን ያስገነዝባል። በተያዘው ጉዲይ አመልካች ያቀረበው ክስ መሰረት ያደረገው ተጠሪዎች የሸጡት ቤትና ይዞታው የራሣቸው አይደለም በሚል ነው።
ስለዚህ የውለታው ጉዲይ ተጠሪዎች ሕጋዊ ባለይዞታ ናቸው ወይስ አይደለም የሚለው በፍሬ ነገር ክርክር እና ማስረጃ የሚጣራ በመሆኑ በዚህ ደረጃ የምንመረምረው አይደለም። የሥር ፍ/ቤት የፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ/2/ን በመመርኮዝ ክሱን በይርጋ ደንብ ስለዘጋው የዚህን አቋም አግባብነት ብቻ እንመረምራለን።
ውል የማፍረስ /invalidation/ መነሻ ምክንያቶች በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 18ዐ8 ተዘርዝረዋል።
እነዚህም ውለ አመሰራረት ላይ የፈቃድ ጉድለት መኖር ከተዋዋይ ወገኖች አንደ ችልታ ማጣት፤
የውለታው ጉዲይ ሕገወጥነት ወይም ኢምራላዊነት ወይም የውለ አቀራረጽ /ፍርም/ በሕግ የተደነገገውን ሥርዓት አለመጠበቅ የሚለ ናቸው።
ከእነዚህ ምክንያቶች በአንደ ወይም በልላው መነሻ ውለ እንዱፈርስ ጥያቄ በማንና መቼ መቅረብ እንዲለበትም በሕጉ ተመልክቷል።
ከዚሁ አንፃር በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ ሥር እንደተመለከተው የውለ መፍረስ ምክንያት ከተዋዋይ ወገኖች ፈቃድ ጉድለት ወይም ችልታ ማጣት ጋር የተያያዘ ከሆነ ውለ እንዱፈርስ ጥያቄ መቅረብ ያለበት በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ መሆን እንዲለበት ያመለክታል።
የጊዜውም አቆጣጠር ውለ የማይረጋበት ምክንያት ከቀረበት ጊዜ ወይም አካለመጠን ከደረሰ ጊዜ ጀምሮ መሆኑንም ተመልክቷል። ይህ የድንጋጌው ይዘት ከፍ ሲል ከተጠቀሱት ምክንያቶች የተወሰኑትን ብቻ ለይቶ ያስቀመጠ መሆኑን መረዲት ይቻላል። ስለሆነም ከፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 18ዐ8/1/ ድንጋጌ ይዘት ጋር ተገናዝቦ ሲታይ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ/1/2/ የተመለከተው የጊዜ ገደብ የሚያገለግለው ውለ በፈቃድ ጉድለት ወይም በችልታ ማጣት መነሻ እንዱፈርስ የሚቀርብ ጥያቄን በሚመለከት ብቻ እንደሆነ መረዲት ይቻላል።
No topics extracted.
ከዚህ ላላ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 18ዐ8/2/ ሥር የተዘረዘሩትን ምክንያቶች መነሻ በማድረግ ውል እንዱፈርስ የሚቀርብ የዲኝነት ጥያቄ በፍ/ብ/ሕግ ድንጋጌ ቁጥር 181ዐ መሰረት በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዱቀርብ ሕጉ አላስገደደም። ስለዚህም የውለታው ጉዲይ ሕጋዊነትን አስመልክቶ የቀረበው ክስ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ መሰረት በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ አልቀረበም ሲል የሥር ፍ/ቤት የደረሰበት ድምዲሜ የሕጉን ይዘት በአግባቡ ያገናዘበ ሆኖ አልተገኘም። ስለሆነም የውለታውን ጉዲይ ሕጋዊነት አስመልክቶ የሚያቀርብ ክስ የይርጋ ጊዜ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ ሥር የሚሸፈን ሣይሆን እንደማናቸውም የውል ጉዲዮች ክርክር በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 1845 በተደነገገው የአሥር ዓመት ጊዜ የሚታይ ይሆናል። በተያዘው ጉዲይ ግራ ቀኙ መካከል የሽያጭ ውል የተደረገው ነሐሴ ወር 199ዐ ዓ.ም ሲሆን ክስ የቀረበው ግንቦት 26 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም ስለመሆኑ ከመዝገቡ ተረድተናል። ጊዜው ሲሰላ ደግሞ አሥር ዓመት /1ዐ/ እንዲላለፈው ተገንዝበናል።
ስለሆነም የውለታው ጉዲይ ሕጋዊነትን አስመልክቶ አመልካች ያቀረበው ክስ በፍ/ብ/ሕግ ቁጥር 181ዐ/2/ መሰረት በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ አልቀረበም በሚል የሥር ፍ/ቤት የሰጠው ብይን ሉታረም የሚገባው ሆኖ ተገኝቷል።
ስለሆነም ተከታዩን ውሣኔ ሰጥተናል።
ው ሣ ኔ
የፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁ. 13325 መስከረም 28 ቀን 2ዐዐ1 ዓ.ም የሰጠው ብይን እና የፋዳራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ. 72117 በዐ2/11/2ዐዐ1 ዓ.ም የሰጠው ፍርድ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 348/1/ መሰረት ተሽሯል።
የአመልካች የዲኝነት ጥያቄ በሁለት ዓመት የይርጋ ጊዜ የሚሸፈን አይደለም ብለናል።
ክሱ የአሥር ዓመት ይርጋ ጊዜ አላለፈበትም ብለናል።
ስለሆነም በግራ ቀኙ የቀረበውን የፍሬ ነገር ክርክር መርምሮ ተገቢውን ውሣኔ እንዱሰጥበት ብለን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 341/1/ መሰረት መዝገቡን ለፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት መልሰናል። ይፃፍ።
ግራ ቀኙ የዚህን ፍ/ቤት ወጪና ኪሣራ የየራሣቸውን ይቻለ ብለናል። መዝገቡ ተዘግቷል ይመለስ።