No summary available.
የካቲት 11 ቀን 2006 ዓ.ም ዳኞች፡- አልማው ወል አላ መሐመድ ረታ ቶሎሳ አዳነ ንጉሤ ሙስጠፋ አህመድ አመልካች፡- አቶ ግርማ ደሳለኝ ቀረቡ።
ተጠሪ፡- ወጣቶች ገነት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ ቤት ነ/ፈጅ አንዋር ሙስጠፋ ቀረቡ።
**
መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል።
**
ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው አመልካች በተጠሪ መሥሪያ ቤት ያላግባብ ከሥራ የተሰናበቱ ስለመሆኑ ገልጸው የተለያዩ ክፍያዎች እንዲከፈላቸው የጠየቁት ዳኝነት በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አግባብ የሚታይ አይደለም ተብሎ ውድቅ በመደረጉ ነው።
አመልካች በተጠሪ መሥሪያ ቤት በጥበቃ ሰራተኛነት ተቀጥረው በመሥራት ላይ እንዳሉ ከሕግ ውጪ ተሰናብቼአለሁ በማለት የተለያዩ ክፍያዎች እንዲከፈሐቸው በፍድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ክስ መስርተው ፍርድ ቤቱ ተጠሪን ጠርቶ ባለመቅረቡ በልለበት አይቶና ጉዳዩን አጣርቶ ጉዳዩን የማየት ሥልጣን የለኝም በማለት የወሰነ ሲሆን፤ ይግባኝ የቀረበለት የፍድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ግራ ቀኙን ከአከራከረ በኋላ የስር ፍርድ ቤትን ውሣኔ አጽንቶታል።
የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም ይህንኑ ውሣኔ በመቃወም ለማስለወጥ ነው። የአመልካች የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ ይዘትም ተጠሪ ትምህርት ቤት ከሕዝብ ትምህርት ቤትነት ወደ መንግሥት ከመዛወሩ በፊት ለሰሩባቸው ጊዜያት ተገቢ ክፍያ እንዲከፈላቸው ዳኝነት የጠየቁ ሆኖ እያለ፤ ትምህርት ቤቱ ወደ መንግሥት ከተዛወረ በኋላ ሥራ ባልሰሩበት ሁኔታ ጉዳዩ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አይታይም ተብሎ መወሰኑ ያላግባብ ነው የሚል ነው። አቤቱታቸውም ተመርምሮ አመልካች ቀደም ሲል ተጠሪ ከሕዝብ ወደ መንግሥት ትምህርት ቤት ሳይቀየር በማገልገል ላይ እያሉ ያላግባብ መሰናበታቸውን ገልፀው በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ መሰረት የቀረበው ክስ ተጠሪ በአሁኑ ወቅት የመንግሥት እንጂ፣ የሕዝብ ተቋም አይደለም ተብሎ በስር ፍርድ ቤቶች ውድቅ የመደረጉን አግባብነት ለመመርመር ሲባል ጉዳዩ ለሰበር ችሎቱ እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ተጠሪ ቀርቦ ግራ ቀኙ በጽሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል። እንዲሁም ለጉዳዩ አግባብነት ያለው መመሪያ እንዲቀርብ ተደርጎ አመልካችም አስተያየት እንዲሰጡበት ተደርጓል።
የጉዳዩ አመጣጥ አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለፀው ሲሆን፣ ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሣኔ እና አግባብነት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ ጉዳዩ ያስቀርባል ሲባል ከተያዘው ጭብጥ አንፃር በሚከተለው መልኩ መርምሮታል።
ከክርክሩ ሂደት መገንዘብ የተቻለው አመልካች በተጠሪ ተቋም ሲሰሩ በነበረበት ጊዜ ተቋሙ የሕዝብ የነበረ መሆኑን፤ ከሐምል 01 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ወደ መንግሥት የተዛወረ መሆኑን ፤ አመልካች ስንብቱ ተከናውኗል በማለት ክስ የመሰረቱት ደግሞ መስከረም 15 ቀን 2005 ዓ.ም መሆኑን፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሕዝብ ጥያቄና ፍላጎት ከሕዝብ ይዞታነት ወደ መንግሥት ይዞታነት የሚዛወሩ የሕዝብ ትምህርት ቤቶችን ሽግግር ለማስፈፀም የተዘጋጀው መመሪያ ደግሞ ተፈፃሚነቱ ከሰኔ 1 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑን ነው።
ወደ ሕጉ ስንመጣ የአዋጅ ቁጥር 377/1996 የራሱ የሆነ የተፈጻሚነት ወሰን ያለው ስለመሆኑ አንቀጽ 3 የሚደነግግ ሲሆን፤ ይህ ድንጋጌ በአዋጁ የሚገዙትና የማይገዙትን የሥራ ግንኙነቶችን ይዞ ይገኛል። የአዋጁ አንቀጽ 31 በንዑስ አንቀጽ 2 ስር በስተቀር የተደነገጉት እንደተጠበቁ ሆነው ይህ አዋጅ በአሰሪና ሰራተኛ መካከል በሚደረግ በቅጥር ላይ በተመሰረተ የሥራ ግንኙነት ላይ ተፈጻሚ እንደሚሆን ያመለክታል። ስለዚህም በቅጥር ላይ የተመሰረተው ግንኙነት በአንቀጹ ንዑስ አንቀጽ 2 ስር ከተዘረዘሩት ውስጥ የሚወድቅ ከሆነ የዚህ አዋጅ ድንጋጌዎች የማይፈጸሙባቸው መሆኑን በአንድ መልኩ ከዚህ ድንጋጌ ስንረዳ በልላ መልኩ ደግሞ ከነዚህ ውጭ ባሉ በአሰሪና ሰራተኛ መካከል በሚፈጠሩ ማንኛውም ግንኙነት ላይ አዋጁ ተፈጻሚነት እንደሚኖረው እንረዳለን። የአንቀጹ ሁለተኛው ንዑስ አንቀጽ ድንጋጌ ደግሞ ግንኙነታቸው በቅጥር ላይ የተመሰረተ ቢሆንም በዝርዝር በሚያስቀምጣቸው የሥራ ግንኙነቶች ላይ አዋጁ የማይፈጸም መሆኑን የሚያመላክት ነው። እነዚህም ለአስተዳደግ ሲባል፣ ከሕመም ለመዳን፣ ወይም እንደገና ለመቋቋም፣ የትምህርትና ለሥልጠና የሙያ መልመጃ ትምህርትን ሳይጨምር የሚደረጉ የሥራ ውሎችን፣ የሥራ መሪን፣ ለትርፍ በሚካሕድ ሥራ ላይ ያልተመሰረተ የግል አገልግሎት ቅጥርን፣ በልዩ ሕግ የሚተዳደሩ እንደ የጦር ኃይል ባልደረቦችን፣ የመንግሥት አስተዳደር ሰራተኞችን፣ ዳኞችን፣ ዐቃቤ ሕጐችን፣ ፖላሶችን እና ልሎችንም እንዲሁም በራሱ የንግድ ሥራ ወይም በራሱ የሙያ ኃላፊነት የሚሰራ ሥራ የሚያከናውን ተዋዋይ ያለበት ግንኙነቶች ናቸው። በመሆኑም አዋጁ እነዚህ ግንኙነቶች ላይ የማይፈጸም መሆኑን ያሳያል።
ስለሆነም በአጭሩ ሲገለጽ አዋጁ በአጠቃላይ በአሰሪና ሰራተኛ መካከል በሚቋቋም በቅጥር ላይ የተመሰረተ የሥራ ግንኙነት ላይ ተፈጻሚነት የሚኖረው ቢሆንም፤ በአዋጁ በግልጽ በተደነገጉ ልላ ሕግ በሚገዛቸው ግንኙነቶች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም።
ወደተያዘው ጉዳይ ስንመለስ አመልካች ተጠሪ ተቋም ወደ መንግሥት ከሐምል 01 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ሲዛወር ከተጠሪ ጋር የሥራ ግንኙነት እንዳልነበራቸው የሚገልጹ ቢሆንም፤
መመሪያው ተፈጻሚ የሆነው ግን ከሰኔ 01 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ በመሆኑ፤ ጉዳዩ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አግባብ የሚታይበት ምክንያት የለም። መመሪያው ወደኋላ ሂዶ እንዲሰራ ላደረግ የሚችልበት የሕግ አግባብ የለም በማለት አመልካች የሚያቀርቡት ክርክርም ሰኔ ወር 2004 ዓ.ም ውስጥ ሥራ ላይ ያልነበሩ መሆኑ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ተቀባይነት ላሰጠው የሚገባ ሆኖ አላገኘንም። እንዲሁም የስር ፍርድ ቤት የአሁኑ ተጠሪ ባልቀረበበት ሁኔታ የሥልጣን ጉዳይ አንስቶና በተገቢው ማስረጃ በማጣራት ዳኝነት መስጠቱም ተካራካሪ ወገን ባይቀርብም ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነትም የስረ ነገር ሥልጣን ጥያቄን ማንሳት የሚችል ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 91 እና 2311ለ ድንጋጌዎች የምንረዳው በመሆኑ፤ በዚህ ረገድ አመልካች የሚያቀርቡት ቅሬታም ተቀባይነት ያለው ሆኖ አልተገኘም። በመሆኑም በአመልካች እና በተጠሪ መካከል ያለው ግንኙነት በአዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 32 እና በአዲስ አበባ ከተማ የመንግሥት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 6/2000 መሰረት በመደበኛው ፍርድ ቤት የሥራ ክርክር ችሎት የሚታይ ባለመሆኑ፤ የበታች ፍርድ ቤቶች ክሱን ውድቅ ማድረጋቸው መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት መፈፀሙን የሚያሳይ ሆኖ አልተገኘም። በዚህም ምክንያት ተከታዩን ወስነናል።
ው ሣ ኔ
በፍድራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ተሰጥቶ በፍድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ ሰኔ 18 ቀን 2005 ዓ.ም በውሣኔ የፀናው ብይን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 3481 መሰረት ጸንቷል።
የአመልካች ክስ በአዋጅ ቁጥር 377/1996 መሰረት የሚገዛ አይደለም ተብሎ ውድቅ መደረጉ ባግባቡ ነው ብለናል።
አመልካች ሥልጣን ባለው አካል ጥያቄያቸውን ከማቅረብ ይህ ውሣኔ አያግዳቸውም ብለናል።
በዚህ ችሎት ለተደረገው ክርክር የወጣውን ወጪና ኪሣራ የየራሳቸውን ይቻሉ ብለናል።
No topics extracted.