No summary available.
ህዳር 16 ቀን 2006 ዓ.ም ዳኞች፡- አልማው ወል ዓላ መሐመድ ረታ ቶሎሳ አዳነ ንጉሴ ሙስጠፋ አህመድ አመልካች፡- ሕጻን ሪያን ሚፍታህ ሞግዚት ወ/ሮ ፋጡማ በሽር ቀረቡ ተጠሪ፡- ኤልሲውዲ ኬብልስ ኃላፊነቱ የተ.የግል ማህበር የቀረበ የለም **
መዝገቡ ተመርምሮ ተከታዩ ፍርድ ተሰጥቷል።
**
በዚህ መዝገብ የቀረበው ጉዳይ የጉዳት ካሳን የሚመለከት ነው።የአመልካች ሞግዚት በፍ/መ/ደረጃ ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ ተጠሪ የከሳሽን እውቅናና ፈቃድ ሳያገኝ የህፃኑን ፎቶ ከሰኔ ወር 2000 ዓ/ም ጀምሮ ለማስታወቂያ ስራ በመጠቀም ግዙፍ የሆነ የማስታወቂያ ሰልዳ በማሰራት ድርጅቱንና የድርጅቱን ምርቶች በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ቦታዎች እና ግብጽን ጨምሮ በተለያዩ ሃያ አምስት ሀገራት በኢተርኔት ሲያስተዋውቅ መቆየቱን፣ይህ ሕገ ወጥ ተግባር በመሆኑ ተገቢውን የካሳ ክፍያ እንዲፈፅም ቢጠየቅም ፈቃደኛ ሳይሆን ቆይቶ በኋላ ላይ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ ብር) ለመክፈል ቢደራደሩም ክፍያው በማስታወቂያ ስራ ከተገኘው ጥቅም ጋር ሲነፃፀር ተመጣጣኝ ያልሆነና አነስተኛ በመሆኑ ከሳሽ ላስማሙ ያለመቻላቸውን ዘርዝረው ከሰኔ ወር 2000 ዓ/ም ጀምሮ እስከ የካቲት ወር 2004 ዓ/ም ለማስታወቂያ ስራ ለተጠቀመው የህፃኑ ፎቶ ብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ) እንዲከፍላቸው ይወሰን ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል።የአሁኑ ተጠሪ ለክሱ በሰጠው መልስም የመጀመሪያ ደረጃ እና የፍሬ ነገር ክርክሮችን ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱንም የተጠሪ በኩል የቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ነጥቦችን ውድቅ አድርጎ በፍሬ ነገር ደረጃ የግራ ቀኙን ክርክርና ማስረጃ ከሰማ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ ተጠሪን ለክሱ ኃላፊ ያደረገው ሲሆን የካሳውን መጠንም በተመለከተም በርትዕ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ) ላሆን እንደሚገባው ወስኖ ይህንኑ የገንዘብ መጠን ተጠሪ ለአመልካች እንዲከፍል ወስኗል።በዚህ ውሳኔ የአሁኑ ተጠሪ ቅር በመሰኘት ይግባኙን ለፍድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረበ ሲሆን የአሁኗ አመልካች ደግሞ የካሳ መጠኑ ላይ ቅር በመሰኘት መስቀለኛ ይግባኝ አቅርበው ፍርድ ቤቱ የአመልካችን መስቀለኛ ይግባኝ ሰርዞ በተጠሪ ይግባኝ ላይ ግራ ቀኙን አከራክሮ ተጠሪ ለክሱ ኃላፊ ተብሎ መወሰኑ ተገቢ ነው በማለት በዚህ ረገድ የተሰጠውን የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ ያፀናው ሲሆን በካሳ መጠኑ ላይ የተሰጠውን የውሳኔ ክፍል ግን በማሻሻል ብር 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) እንዲሆን ወስኗል።የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም በጉዳዩ ላይ ካሳን በተመለከተ ሁለቱም የበታች ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ያለበት ነው በሚል ምክንያት ሲሆን አቤቱታው ተመርምሮም በሰበር ችሎቱ እንዲታይ በመደረጉ ለተጠሪ ጥሪ ተደርጎለት ቀርቦ ግራ ቀኙ በፅሑፍ እንዲከራከሩ ተደርጓል።
የክርክሩ አመጣጥ አጠር ባለመልኩ ከላይ የተገለፀ ሲሆን ይህ ችሎትም የግራ ቀኙን ክርክር ለሰበር አቤቱታው መነሻ ከሆነው ውሳኔ እና አግባብት ካላቸው ድንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ አቤቱታ የቀረበበት ውሳኔ መሰረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት ያለበት መሆን ያለመሆኑን እንደሚከተለው መርምሯል።
ከፍ ሲል እንደተመለከትነው ተጠሪ የህጻኑን ፎቶ ለማስታወቂያ ስራ የተጠቀመበት ስለመሆኑና ይህንንም ሲያደርግ ከሕፃኑ ሞግዚት ተገቢውን ፈቃድ ያላገኘ መሆኑ እንዲሁም በማስታወቂያው ተጠሪ የኤልክትሪክ ኬብል ምርቶችን በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች በሰልዳ ለጥፎ ማስታወቁን፣በግብጽና በልሎች ሃያ አምስት ሃገራት በኢንተርኔት ሲያስተዋውቅም የሕፃኑን ፎቶ ጥቅም ላይ ያዋለ መሆኑ ፍሬ ነገርን የማጣራትና ማስረጃን የመመዘን ስልጣን ባላቸው ፍርድ ቤቶች ተረጋግጧል።ተጠሪም ቢሆን በዚህ ረገድ በበታች ፍርድ ቤቶች የተደረሰው ድምዳሜ ስርዓቱን ጠብቆ በበላይ ፍርድ ቤት ስለመቀየሩ ገልጾ ያቀረበው ክርክር የለም።ስለሆነም ተጠሪ የህጻኑን ፎቶ ለኤልክትሪክ ኬብል ምርቶቹ ለማስተዋወቅ ያለሕፃኑ ሞግዚት ፈቃድ መጠቀሙ የተረጋገጠ ጉዳይ ነው።እንዲህ ከሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 27 ድንጋጌ ስር ባለፎቶግራፉ ወይም ባለስዕሉ ካልፈቀደ በቀር የማንም ሰው ፎቶግራፍ ወይም ስዕል በሕዝብ አደባባይ ላለጠፍም ሆነ ላባዛ ወይም ላሸጥ እንደማይቻል የተመለከተ በመሆኑና በፍ/ሕ/ቁጥር 28 ስር የተመለከተው ልዩ ሁኔታ ስለመኖሩም ተጠሪ ጠቅሶ ያቀረበው ክርክርና ማስረጃ የልለ በመሆኑ የሕፃኑ ፎቶ ጥቅም ላይ ለዋለበት የማስታወቂያ ስራ ተጠሪ ካሳ የማይከፍልበት ህጋዊ ምክንያት የለም።በዚህ ሰበር አከራካሪ የሆነው የከሳ መጠኑ ሲሆን ካሳው የሚከፈልበትን አግባብ በተመለከተ ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት ያለው የሕጉ ክፍል በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 29(2) ድንጋጌ ስር አስፍሯል።በዚህ ድንጋጌ መሰረት በርትዕ አስፈላጊ ሁኖ ሲታይ ስዕሉን በአደባባይ በመለጠፍና በመሸጥ የተጠቀመው ሰው በዚሁ ምክንያት ያገኘው ሀብት ተመዛዛኝ በሚሆንበት መጠን ዳኞች ካሳ እንዲከፍል ላወስኑበት እንደሚችሉ ተደንግጓል።ከዚህ አንጻር ጉዳዩን ስንመለከተው የስር ፍርድ ቤት ተጠሪ የካሳውን መጠን ክዶ በመከራከሩና አመልካችም በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 2141 በተመለከተው አግባብ ትክክለኛውን የካሳ መጠን በማስረጃ ያለማስረዳታቸውን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 29(2) በተሰጠው ስልጣን መሰረት የካሳውን መጠን ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እንዲሆን የወሰነ ሲሆን አመልካች በዚህ ውሳኔ ቅር በመሰኘትም በስርዓቱ መሰረት የመስቀለኛ ይግባኝ አቅርበው ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የካሳ መጠኑን የሕጻኑ ፎቶ በማስታወቂያው ከተገለፁት የምርት አይነቶች ጋር የሚኖረውና ላያስገኝ ከሚችለው ጥቅም አንፃር፤ከነባራዊው ሁኔታ በመነሳት በመመርመር በስር ፍርድ ቤት የተወሰነው የካሳ መጠን የባዛ ሁኖ ማግኘቱን ጠቅሶ ብር 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ) የካሳ መጠን ላሆን እንደሚገባ ወስኗል።ይህ የበታች ፍርደ ቤቶች የካሳ ውሳኔ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 29(2) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ ይዘትና መንፈስ መሰረት ያደረገ ነው ከሚባል በስተቀር የሚነቀፍበት አግባብ የለም።የአመልከች የመስቀለኛ ይግባኝም በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ታይቶ ተቀባይነት ያጣ መሆኑን የክርክሩ ሂደት ያሳያል።ይህም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 340 እና 337 ድንጋጌዎች ስር የተመለከተውን የክርክር አመራርና የዳኝነት አሰጣጥ ስርዓት የተከተለ መሆኑን ከሚያስገነዝብ ውጪ የአመልካች የመስቀልኛ ይግባኝ ሳይታይ የታለፈ ነው ለማለት የማያስችል በመሆኑ በዚህ ረገድ የስር ፍርድ ቤት የሰጠው ትእዛዝም የሚነቀፍ ሁኖ አልተገኘም።ሲጠቃለልም ካሳን አስመልክቶ በጉዳዩ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ለጉዳዩ ቀጥተኛ ተፈፃሚነት ያላቸውን የጉዳት ካሳ ድንጋጌዎችን ያላገናዘበና መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ለማለት ስላልተቻለ ተከታዩን ወስነናል።
No topics extracted.