No summary available.
የሰ/መ/ ህዳር 06 ቀን 2005 ዓ.ም.
ዳኞች፡- ተሻገር ገ/ስላሴ አልማው ወል ዓላ መሐመድ አዳነ ንጉሤ መኰንን ገ/ሕይወት አመልካች፡- የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዐ/ሕግ - አልቀረበም ተጠሪ፡- እብካለ እንዳሻው ጠ/ንግድ ኃ.የተ.የግል ማህበር - አልቀረበም መዝገቡ የተቀጠረው የቅጣት ውሣኔ ለመስጠት ተብሎ ሲሆን የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት ከሕግ ጋር በማገናዘብ መርምረን ተከታዩን የቅጣት ውሣኔ ሰጥተናል።
ቅ ጣ ት ተጠሪ አዋጅ ቁጥር 285/1994 አንቀጽ 56/1/ን የተላለፈ ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አጥፊ ተገቢውን ቅጣት ማግኘት አለበት። ቅጣት የሚወሰነው ደግሞ በወ/ሕ/አንቀጽ 88/2/ ስር ያሉትን ድንጋጌዎች መሰረት በማድረግ ነው። ይህ ችሎትም እነዚህን ሁኔታዎች ተመልክቷል፣ አመዛዝኗልም።
ተጠሪ ሕጋዊ ሰውነት ያለው አካል ሲሆን ጥፋተኛ የተባለበት የወንጀል ድርጊት የሚያስቀጣው ከብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) በማያንስ እና ከብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር) በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከሁለት እስከ አምስት አመት በሚደርስ እስራት መሆኑን አዋጅ ቁጥር 285/1994 በአዋጅ ቁጥር 609/2001 እንደተሻሻለ ያሳያል። በተጠሪ አይነት ሰው ላይ ቅጣት የሚወሰንበትን አግባብ ደግሞ የወንጀል ሕጉ በአንቀጽ 90 መሰረት መሆኑን የወንጀል ህጉ የሚገልፅ ሲሆን የሕግ ሰውነት ባለው አካል ላይ የገንዘብ ቅጣት እና እስራት በሚጣልበት ጊዜ የእስራት ቅጣቱ ሁኔታ ወደ ገንዘብ በመቀየር መሆኑን የአንቀጹ ንዑስ ቁጥር ሶስት ድንጋጌ ይገልፃል። በዚህ ድንጋጌ መሰረት እስከ አምስት አመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል እስከ ብር አስር ሺህ፣ እስከ አምስት ዓመት ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ እስከ ብር ሃያ ሺህ፣ እስከ አስር ዓመት ለሚያስቀጣ እስከ ብር ሃምሳ ሺህ፣ ከአስር ዓመት በላይ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል በአንቀጹ ንዑስ አንቀጽ እስከተመለከተው ከፍተኛ ወሰን ማለትም እስከ ብር አምስት መቶ ሺህ ድረስ የገንዘብ መቀጮው ላደርስ እንደሚችል ሕጉ ያሣያል። እንዲሁም የገንዘብ ቅጣትም በንዑስ ቁጥር አራት ድንጋጌ እንደተደነገገው እስከ አምስት እጥፍ እንደሚደርስ በግልጽ ተቀምጧል። በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 90/3/ ድንጋጌ መሰረት እስከ አምስት ዓመት ላደርስ የሚችል ጽኑ እስራት እስከ ብር 20,000.00 ድረስ የገንዘብ ቅጣት እንደሚቀየር ተደንግጓል። በመሆኑም የተጠሪን የድርጊት አፈፃፀም ስንመለከተው ቀላል ተብሎ ላመደብ የሚገባ በመሆኑ በአመልካች ላይ ላጣል የሚገባው የገንዘብ መቀጮ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ ሁኖ የእስራት ቅጣቱን ደግሞ የሁለት አመት ጽኑ እስራት ሁኖ አግኝተናል። ይህ የሁለት አመት ጽኑ የእስራት ቅጣት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 90/3/ በተደነገገው ስልት መሰረት ወደ ገንዘብ ሲቀየር የሚመጣው ብር 8,000.00 በመሆኑ እና ይህ ከገንዘብ መቀጮ ከብር 10,000.00 ጋር ሲደመር የሚመጣው ውጤት ብር 18,000.00 /አስራ ስምንት ሺህ ብር/ ተጠሪን የሚያርም፣ ልሎችን የሚያስተምርና የሚያስጠንቀቅ ሁኖ አግኝተናል። በመሆኑም ተጠሪ ይህንኑ ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንዲያደርግ፣ አመልካችም ተከታትሎ እንዲያስፈፅም ብለናል።
No topics extracted.