No summary available.
ሐምል ዐ4 ቀን 2004 ዓ.ም.
ዳኞች፡- ተገኔ ጌታነህ አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ ነጋ ደፍሣ አዲነ ንጉሴ አመልካቾች፡-
ጉዲዩ የቀረበው አመልካቾች ከላይ ቁጥራቸው በተገለፁት የሰበር መዛግብት የፋዳራል የመጀመሪያው ፍ/ቤት የሰጠውን የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሳኔ ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት ማፅናቱ መሰረታዊ ህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዱታረምልን በማለት በተናጠል ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ አጣርቶ ለመወሰን ነው። ጉዲዩ በመጀመሪያ የታየው በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው። በፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካቾች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል።
የክርክሩ መነሻ ተጠሪ በአመልካቾችና በዚህ ክርክር ተሳታፉ ባልሆኑ ላልች አምስት ተከሳሾች ላይ መጋቢት 12 ቀን 2003 ዓ.ም ፅፍ ያቀረበው የወንጀል ክስ ነው። ተጠሪ ለስር ፍ/ቤት ባቀረበው የወንጀል ክስ ፣ አመልካቾች በወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና አንቀጽ 703 የተመለከተውን በመተላለፍ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) የስራ አመራር በመሆን በተለያየ ደረጃ በሚሰሩበት ወቅት እንደ አውሮፕዊያን አቆጣጠር ከኦክቶበር 2009 ዓ.ም እና ዱሴንበር 2009 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የውጭ ምንዛሬ አጠቃቀምና አፈቃቀድ ጉድለት በመፈፀም በአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) ላይ ጉዲት አድርሰዋል በማለት የቀረበው የወንጀል ክስ ሲሆን ዝርዝሩም ሲታይ የሚከተለው ይዘት ያለው ነው።
በሥር ፍ/ቤት አንደኛ ተከሳሽ የሆኑት አንደኛው አመልካች አቶ ለይኩን ብርሃኑ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) ፔሬዚዲንት ሆኖ ሲሰራ በለገሀር ቅርንጫፍ ፣ በአዱስ ከተማ ቅርንጫፍ ፣ በሀብተ ጊዮርጊስ ቅርንጫፍና ፣ በመርካቶ ቅርንጫፍ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያ ከውጭ ምንዛሬ አፈቃቀድ ፣ አሰጣጥ ፣ አጠቃቀምና አጠያየቅ ጋር በተያያዘ የተፈፀመው ወንጀልች እያወቀ በአዋጅ ቁጥር 592/2000 ዓ.ም በሚጥስ ሁኔታ የውጭ ምንዛሬ አፈቃቀድና አጠቃቀም እንዱካሄድ በማድረግና የግል ባንኮች መያዝ ፣ የሚገባቸውን የውጭ ምንዛሬ መጠን በተመለከተ ከብሓራዊ ባንክ የወጣውን መመሪያ በመተላለፍ የውጭ ምንዛሬ በመያዝ ፣ ማውጣት የሚገባውን የአሰራር ሥርዓትና መመሪያ ባለማውጣት የወጡ ፣ መመሪያዎች ሲጣሱ የእርምት እርምጃ ባለመወሰደ ፣ የውጭ ምንዛሬ ደንበኞች ተራ ቅደም ተከተል ሉጣስና በቅድሚያ የውጭ ምንዛሬ ሉሰጣቸው የማይገቡ ግለሰቦች እያወቀ ባለመስተካከለና የባንኩ ቋሚ ሰራተኞች የውጭ ምንዛሬ ሲወስደ እያየ እርምጃ ባለመውሰድ የስራ አመራር ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈፅሟል።
በስር ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ሁለተኛ አመልካች አቶ ምትኩ አቦሽ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) ምክትል ፔሬዚዲንት የባንኩ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያ ኃላፉ ሆኖ ሲሰራ ፣ በለገሀር ቅርንጫፍ ፣ በአዱስ ከተማ ቅርንጫፍ ፣ በሀብተጊዮርጊስ ቅርንጫፍ እና በመርካቶ ቅርንጫፍች በውጭ ምንዛሬ አፈቃቀድና አሰጣጥ የተፈፀሙ ጉድለቶችን ባለመስተካከለና በባንኩ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያ ኃላፉ ሆኖ ሲሰራ ያለ ኮሚቴው ፈቃድ በግል ትዕዛዝ የውጭ ምንዛሬ ግዥ ፈቃድ በመስጠት ፣ የውጭ ምንዛሬ ያለቅደም ተከተል ለሰዎች እንዱፈቀድላቸው ሲደረግ ባለመስተካከለ ባንኩ በብሓራዊ ባንክ እንዱይዝ ከተፈቀደለት የውጭ ምንዛሬ መጠን በላይ 28,974,000 (ሃያ ስምንት ሚሉዮን ዘጠኝ መቶ ሰባ አራት ሺህ) የአሜሪካን ድላር ይዞ በመገኘቱና ከዚህ ውስጥ 14,473,000 ድላር/ብር ለብሓራዊ ባንክ ሪፕርት ሣይደረግና ሣይመዘገብ እንዱያዝ ያደረገ በመሆኑ የውጭ ምንዛሬ ሉፈቀድላቸው የሚገባቸውን የባንኩን ደንበኞች በመከልከል የውጭ ምንዛሬ ሉፈቀድላቸው በማይገባቸው ሰዎች የውጭ ምንዛሬ በመስጠት በስራ አመራር ሂደት ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈፅሟል።
በስር ፍ/ቤት አምስተኛ ተከሳሽ የሆነው ሶስተኛው አልካች አቶ ጌታሁን አላመረ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) የአዱስ ከተማ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ሲሰራ ከባንኩ መመሪያ ውጭ የውጭ ምንዛሬ ለግለ በመፍቀድ ለግል ጥቅሙ በማዋለና ለባንኩ ደንበኞች በበላይ የስራ ኃላፉዎች የተፈቀደውን የውጭ ምንዛሬ ለላልች ላልተፈቀደላቸው ሰዎች በመስጠት በስራ አመራር ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈፅሟል።
በስር ዘጠኛ ተከሳሽ የሆነው አራተኛው ተከሳሽ አቶ ቸርነት ዋጋሪ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ መርካቶ ቅርንጫፍ የውጭ ንግድ ክፍል ኃላፉ ሆኖ ሲሰራ የውጭ ምንዛሬ ኮሚቴ ያልተፈቀደላቸውን ደንበኞች በማስተናገድ ፣ የደንበኞችን የምዝገባ ቅደም ተከተል ሣይጠበቅ ያለምዝገባ ተራቸው ላልች ግለሰቦች የውጭ ምንዛሬ እንዱያገኙ በማድረግ በስራ አመራር ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈፅሟል።
በስር ፍ/ቤት ስድስተኛ ተከሳሽ የሆነው አምስተኛው አመልካች አቶ እንዲለ ቴድ የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ የአዱስ ከተማ ቅርንጫፍ የውጭ ንግድ ክፍል ኃላፉ ሆኖ ሲሰራ የውጭ ምንዛሬ የተፈቀደላቸውን የባንኩን ደንበኞች በመከልከል ላልተፈቀደላቸው ግለሰቦች የውጭ ምንዛሬ በመስጠት የስራ አመራር ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈፅሟል ፣ የሚል ክርክር ይዘት ያለው የወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።
ተጠሪ የቀረበው የወንጀል ክስ ኮፑ ለአመልካቾች ደርሷቸው የመጀመሪያ የክስ መቃወሚያ ያቀረቡ ቢሆንም የሥር ፍ/ቤት የአመልካቾችን የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ውድቅ አድርጎባቸዋል። አመልካቾች የወንጀለን ድርጊት አልፈፀምንም ጥፊተኞች አይደለንም በማለት ክደው በመከራከራቸው ፣ ተጠሪ ዘጠኝ ምስክሮች በማቅረብ የምስክርነት ቃላቸውን እንዱሰጡ ያደረገ ሲሆን የወንጀለን ድርጊት ያስረዲለ የሚላቸውን የፅሁፍ ማስረጃዎች አቅርቧል።
ተጠሪ በስር ፍ/ቤት ለምስክርነት አቅርቦ ካሰማቸው ምስክሮች ውስጥ ሁለቱ የአዋሽ ባንክ አክሲዮን ማህበር የአስተዲደር ቦርድ አባላት ፣ ሶስቱ ደግሞ በባንኩ ውስጥ ከፍተኛ የአክሲዮን ድርሻ ካላቸው አስር ባለሀብቶች የተወከለ መሆናቸውን ገልጸው ባንኩ በውጭ ምንዛሬ አያያዝ ፣ አፈቃቀድና አጠቃቀም ችግር ያለበት ስለመሆኑ የደረሳቸውን መረጃ ለማጣራት ኮሚቴ የተቋቋመ መሆኑን አስረድተዋል። ምስክሮች ከቦርድ አባላትና ከባለመብቶች የተወጣጡ ኮሚቴዎች በአንድነት በባንኩ ሥራ አመራር በኩል የተፈፀሙ ተግባራት ሲያጣሩ ፣ ባንኩ በብሓራዊ ባንክ እንዱያዝ የተፈቀደለት የውጭ ምንዛሬ የካፑታለ 15% ብቻ መሆን ሲገባው ከዚያ በላይ ድላር ይዞ መገኘቱንና በዚህ ምክንያት በብሓራዊ ባንክ ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር) የተቀጣ መሆኑን፣ ሁለተኛ አመልካች ያለውጭ ምንዛሬ ኮሚቴ ፈቃድ በግለ ለግለሰቦች ያለተራቸው የውጭ ምንዛሬ እንዱሰጣቸው ትዕዛዝ የሰጠ መሆኑን ፣ በአዋሽ ባንክ ለገሀር ፣ አዱስ ከተማ ፣ ሀብተጊዮርጊስ ድልድይና በመርካቶ ቅርናጫፍ የውጭ ምንዛሬ የአፈቃቀድና አጠቃቀም ከፍተኛ ችግር የነበረበት ፣ ተመዝጋቢው ተራ የሚጠብቁ ሰዎች የውጭ ምንዛሬ ሳያገኙ ያልተመዘገቡና የባንኩ ደንበኛ ላልሆኑ ሰዎች የውጭ ምንዛሬ የተሰጠ መሆኑን ፣ አንደኛ አመልካች ይህንን ችግር በማስተካከል ማድረግ የሚገባውን ተግባር ያለመፈፀሙንና ለችግሩ መከሰት አመልካቾች የነበራቸውን ሚና በመዘርዘር መሥክረዋል። ምስክሮቹ አንደኛ አመልካች ተገቢውን የአሰራር ስርዓት ባለመዘርጋቱና ማውጣት የሚገባውን መመሪያ ባለመወጣቱ ሁለተኛው አመልካች በኃላፉነት የተሰጠውን ተግባር በአግባቡ ካለማውጣቱ በተጨማሪ ዲንኤል ለተባለ የባንኩ ሰራተኛ ለእሱ ፀሐፉ የውጭ ምንዛሬ እንዱወስደ ፈቅድ የተገኘ መሆኑን ባደረጉት ማጣራት እንደተገነዘቡ የመሰከሩ መሆኑን ከሥር ፍርድ ቤት ውሣኔ ተረድተናል።
ተጠሪ በስር ፍ/ቤት ያቀረባቸው ዘጠነኛ ምስክር የባንኩ ኢንስፓክሽን መምሪያ ኃላፉ ሲሆኑ ተጠሪ በስር ፍ/ቤት ያቀረባቸውን ስድስተኛ ሰባተኛና ስምንተኛ ምስክሮች የባንኩ ኢንስፓክሽን ሰራተኞች መሆናቸውን ገልጸው፣ ተጠሪ በወንጀል ክሱ በገለጸው ጊዜ ውስጥ በባንኩ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መመሪያና በለገሀር ፣ አዱስ ከተማ ፣ ሀብተጊዮርጊስ ድልድይና መርካቶ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ አፈቃቀድና አጠቃቀም በማጣራት የፅሐፍ ሪፕርት እንዲቀረቡ ገልፀው አንደኛው አመልካች በውጭ ምንዛሬ በመፍቀድ ያልተሳተፊ መሆኑንና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ሲያጋጥም ሁለተኛ አመልካች ሰብሳቢ በሥር ፍርድ ቤት ሁለተኛና ሶስተኛ ተከሣሽ የነበሩትና በዚህ ክርክር ተሳታፉ ያልሆኑት የኮሚቴው አባል ሆነው የውጪ ምንዛሬ ኮሚቴ መቋቋሙን ፣ ነገር ግን በመምሪያውና በአራቱ የባንኩ ቅርንጫፍች የውጭ ምንዛሬ አጠቃቀምና አፈቃቀድ ከፍተኛ ችግር የነበረበት መሆኑን እንዲረጋገጡ ምስክሮች ለሥር ፍርድ ቤት ከሰጡት የምስክርነት ቃል ተረድተናል። ከዚህ በተጨማሪ ምስክሮቹ በመምሪያውና በአራቱ ቅርንጫፍች ያለውጭ ምንዛሬ ኮሚቴ ውሣኔ ለሁለተኛ አመልካች ለሶስተኛ አመልካች ለአራተኛ አመልካችና ለአምስተኛ አመልካች የውጭ ምንዛሬ ሰጥተው ያገኙ መሆኑን ፣ ሁለተኛው አመልካች ያለውጭ ምንዛሪ ኮሚቴ ውሣኔ በግለ በርካታ የውጪ ምንዛሬ መፍቀጃ ቅፆች ላይ ፈርሞ ያገኙት መሆኑና መምሪያውና አራቱ ቅርንጫፍች የውጭ ምንዛሬ በማግኘት ተመዝግበው ተራ ለሚጠብቁ ደንበኞች የውጪ ምንዛሬ ሣይሰጡ ተመዝግበው ተራ ላልያዙና የባንኩ ደንበኛ ያልሆኑ ሰዎችን በማስቀደም የውጭ ምንዛሬ የሰጡ መሆኑን እንዲረጋገጡ ከሥር ፍርድ ቤት ውሣኔ ተረድተናል።
ተጠሪ የወንጀል ክሱን ለማስረዲት ባቀረበው የሰነድ ማስረጃ ሁለተኛው አመልካች የውጪ ምንዛሬ ካሚቴ ውሣኔ ሳይሰጥበት በግለ 9,280,755 /ዘጠኝ ሚሉዮን ሁለት መቶ ሰማኒያ ሺህ ሰባት መቶ ሀምሳ አምስት /የአሜሪካን ድላር 2,938,535 ዩሮ /አንድ ሚሉዮን ዘጠኝ መቶ ሰላሣ ስምንት ሺህ አምስት መቶ ሰላሣ አምስት / ዮሮ እና 50,060/ ሃምሣ ሺህ ስልሣ / የእንግሉዝ ፕዉንድ የፈቀደ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑንና የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ለገሀር ቅርንጫፍ ከፈቀደው 6,196,760.88 /ስድስት ሚሉዮን አንድ መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ስልሣ/ የአሜሪካን ድላር ውስጥ 2,125,725.04 /ሁለት ሚሉዮን አንድ መቶ ሃያ አምስት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ አምስት ከዜሮ አራት/ የአሜሪካን ድላር አለመከፈለን ሶስተኛ አመልካች ሥራ አስኪያጅ አምስተኛው አመልካች የውጭ ንግድ ክፍል ኃላፉ ሆነው ሲሰሩበት የነበረው የአዱስ ከተማ ቅርንጫፍ ለሶስተኛ አመልካች የንግድ ድርጅት የፈቀደው 426,792/አራት መቶ ሃያ ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ዘጠና ሁለት/ የአሜሪካን ድላር አለመከፈለን አራተኛው አመልካች የውጪ ንግድ ክፍል ኃላፉ በመሆን ሲሰራበት የነበረው መርካቶ ቅርንጫፍ ከፈቀደው የውጪ ምንዛሬ 299,760 /ሁለት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ሰባት መቶ ሥልሣ የአሜሪካን ድላር / አለመከፈለን በአጠቃላይ በዚህ ሂደት ብር 3,154,328 /ሶስት ሚሉዮን አንድ መቶ ሃምሣ አራት ሺህ ሶስት መቶ ሃያ ስምንት የአሜሪካን ድላር በህገ ወጥ መንገድ በውጭ ምንዛሬ ተሰጥቶ ለባንኩ ያልተመለሰ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ በዚህ ወንጀል በዚህ ክርክር ተሳታፉ ያልሆኑትና ተከሣሾች ስማቸው ከተራ ቁጥር 2 እስከ ተራ ቁጥር 5 የተገለፀው አመልካቾች ኃላፉነት ያለባቸው መሆኑን የሰነድ ማስረጃው እንደሚጠቁም ከሥር ፍርድ ቤት ውሣኔ ለመገንዘብ ችለናል።
አመልካቾች በተጠሪ የወንጀል ክስ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት የፈፀመ መሆኑን የሚያረጋግጥ በቂ ማስረጃ ተጠሪ ያቀረበ መሆኑን በመግለፅ አመልካቾች የመከላከያ ማስረጃ እንዱያቀርቡ የሥር ፍርድ ቤት በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 142 መሰረት ብይን ሰጥቷል። የሥር ፍርድ ቤት በሰጠው ብይን መሰረት አንደኛ አመልካች በተከሰሱበት የወንጀል ድርጊት ያልፈፀሙና በኃላፉነትም ልጠየቅ የማይገባኝ መሆኑን ያስረደልኛል ያሎቸውን አራት የመከላከያ ምስክሮች አቅርበው ያስመሰከሩ መሆኑን ከሥር ፍርድ ቤት ውሣኔ ተረድተናል። እንደዚሁም አንደኛ አመልካች የሰነድ ማስረጃዎችን በመከላከያ ማስረጃነት እንዲቀረቡ የሥር ፍርድ ቤት በውሣኔው ውስጥ አስፍሮታል። ሁለተኛው አመልካች በበኩለ በነበረው ኃላፉነት የፈፀማቸው ተግባራት የሥራ አመራር ጉድለት አለመሆናቸውን የሚያስረደ ሶስት የመከላከያ ምስክሮች አቅርቦ ያሰማ መሆኑንና የሰነድ ማስረጃ የቀረበ መሆኑን ሶስተኛና አምስተኛው አመልካች በጋራ አምስት የመከላከያ ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃ በመከላከያ ማስረጃነት ያቀረቡ መሆኑን ፣ አራተኛው አመልካች አራት የመከላከያ ምስከሮችንና የሰነድ ማስረጃ በመከላከያ ማስረጃነት ያቀረቡ መሆኑን ከሥር ፍርድ ውሣኔ ተገንዝበናል። የሥር ፍርድ ቤት የተጠሪንና የአመልካቾችን ማስረጃ ከመረመረና ከመዘነ በኋላ አንደኛ አመልካች በባንኩ ኃላፉና የሥራ መሪ ሆነው እያለ ሥራዎችን ለሁለተኛ አመልካች በውክልና ከሰጡ በኋላ የተለያዩ ችግሮች እየተፈጠረ ስለመሆኑ ጥቆማ የደረሳቸው መሆኑንና ሀሜትና አለባልታ ናቸው እያለ በማለት በዝምታ በማለፍ በባንኩ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያና በአራቱ ቅርንጫፍች በተከሰተው ብልሹ አሰራር ምክንያት በባንኩ ላይ ለደረሰው ጉዲት በተሰጠው ኃላፉነት መሰረት የመቆጣጠር የመከታተልና የባንኩን ሥራ የመምራት ኃላፉነት ባለመወጣቱ ተጠሪ /ዐቃቤ ሕግ / በወንጀል ክሱ የተገለፀውን የህግ ድንጋጌ በመተላለፍ ወንጀል የፈፀመ ጥፊተኛ ነው በማለት በአንድ ዓመት ከሶስት ወር ፅኑ እስራትና በብር 1ዐ,ዐዐዐ/አስር ሺህ ብር / መቀጮ እንዱቀጡ ውሣኔ ሰጥቷል።
የሥር ፍርድ ቤት ሁለተኛ አመልካች ተጠሪ በወንጀል ክሱ የዘረዘራቸው የውጭ ምንዛሬ አጠቃቀምና አፈቃቀድ ችግሮችን የፈፀሙ መሆኑን በሰውና በፅሐፍ ማስረጃ ያረጋገጠበት በመሆኑና ሁለተኛው አመልካች ያቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ይህንን የማያስተባበል መሆኑን ገልፆ ሁለተኛ አመልካች ተጠሪ የተጠቀሰውን የህግ ድንጋጌ በመተላለፍ ወንጀል የፈፀሙ ጥፊተኛ ናቸው በማለት በአንድ ዓመት ከሶስት ወር ፅኑ እስራትና በብር 10,000/አስር ሺህ ብር መቀጮ/ እንዱቀጡ ወስኗል። ሶስተኛ አመልካችና አምስተኛው አመልካቾች በተከሰሱበት ወንጀል ጥፊተኛ ናቸው በማለት በሁለት ዓመት ከሁለት ወር ፅኑ እስራትና በብር 15,ዐዐዐ/አስራ አምስት ሺህ ብር/ እንዱቀጡ የወሰነ ሲሆን አምስተኛው አመልካች በተከሰሱበት ወንጀል ጥፊተኛ ነው ብል በአንድ ዓመት ከሶስት ወር ፅኑ እስራትና በብር 1ዐ,ዐዐዐ/አስር ሺህ ብር/ መቀጮ እንዱቀጡ ውሣኔ ሰጥቷል።
አመልካቾች የሥር ፍርድ ቤት የሰጠውን የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ በመቃወም ይግባኝ ለፋደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተናጠል በተለያዩ መዝገቦች አቅርበዋል። የፍደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ የሥር ፍርድ ቤት የሰጠውን የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ አፅንቶታል።
አመልካቾች የሥር ፍርድ ቤትና ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሰጡት የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት መሆኑን በመግለፅ አንደኛ አመልካች በሰበር መዝገብ የሰበር አቤቱታ አቅርበው ተጠሪ በሰበር አቤቱታው መልስ የሰጠበት ሲሆን ሁለተኛው አመልካች በዚህ መዝገብ ላቀረቡት የሰበር አቤቱታ ሶስተኛ አመልካች በሰበር መዝገብ ላቀረበው የሰበር አቤቱታ ፣ አራተኛ አመልካች በሰበር መዝገብ ላቀረበው የሰበር አቤቱታና አምስተኛ አመልካች በሰበር መዝገብ ላቀረበው የሰበር አቤቱታ ተጠሪ በዚህ መዝገብ በማጠቃለል ግንቦት 28 ቀን 2ዐዐ4 ዓ.ም የተፃፈ መልስ አቅርቧል። አመልካቾች በየግላቸው የመልስ መልስ አቅርበዋል።
አመልካቾች በተለያዩ መዝገቦች ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ ይዘት ተመልክተናል። አመልካቾች ሆነ ብለንና አስበን የአዋሽ ኢንተርናችናል ባንክ /አ.ማ/ ላይ ጉዲት ለማድረስ የፈፀመነው የወንጀል ድርጊት ስለመኖሩ ተጠሪ በማስረጃ አላረጋገጠም። በአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር ላይ የደረሰ ጉዲት መሆኑ በተጠሪ ማስረጃ አልተረጋገጠም አንድ ሰው በወንጀል የሚጠየቀው የግዙፍ ተግባር የሞራልና የህግ ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ መሆኑን በወንጀል ህጉ አንቀፅ 23 ንዐስ አንቀፅ 2 በግልፅ የተደነገገ ከመሆኑም በላይ ይህ ሰበር ችልት በተመሣሣይ ጉዲይ ከዚህ በፉት አስገደጅ የህግ ትርጉም ሰጥቶበታል። አመልካቾች የፈፀምነው ግዙፍ የወንጀል ድርጊት ያለ መሆኑና የወንጀል ሃሣብ / ሞራላዊ ሁኔታ መኖር ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ጥፊተኛ ተብለን መቀጣታችን መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው። እንደዚሁም ተጠሪ እኛ ፈፅምነው በተባለው ድርጊትና በአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ / አ.ማ/ ላይ ደርሷል በሚለው ጉዲት መካከል የድርጊትና የውጤት ግንኙነት መኖርን አላስረዲም። አመልካቾች በተጠሪ የቀረበውን ክስና ማስረጃ በመከላከያ ማስረጃችን አስተባብለን እያለን ጥፊተኛ መባላችን መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው። የሥር ፍርድ ቤት ከአመልካቾች ጋር ተመሣሣይ ወንጀል ድርጊት ፈፅማችኋል ተብለው የጥፊተኝነት ውሣኔ የተሰጠባቸው ተከሣሾች ላይ ያስተላለፈውን የቅጣት ውሣኔ ሲገድብ በእኛ ላይ የወሰነው የቅጣት ውሣኔ አለመገደቡ መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ እንዱታረምልን የሚል ይዘት ያለው ሆኖ አግኝተነዋል። ተጠሪ በበኩለ አመልካቾች ሆነ ብለው ጊዚያዊና ሰው ሰራሽ የውጪ ምንዛሬ እጥረት እንዱፈጠር ድርጊቱን መፈፀማቸው በሰውና በፅሐፍ ማስረጃ ተረጋግጧል። አንደኛ አመልካችም ማድረግ የሚገባቸውን ጥንቃቄ ባለማድረግና የባንኩ የበላይ አመራር በመሆናቸው መፈፀም የሚገባቸውን ተግባር ያልፈፀሙ መሆኑ በማስረጃ ተረጋግጧል። አመልካቾች በባንኩ ላይ የደረሱትን ጉዲት በገንዘብ በሚተመን መንገድ ብቻ ሣይሆን በባንኩ አገልግልት አሰጣጥ ላይ ጉዲት ያደረሱ መሆኑን አረጋግጠናል። ስለሆነም አመልካቾች በግዙፍ ተግባርና የሞራል ሁኔታ አልተሟላም በማለት ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ የህግ መሰረት የላለው ነው። አመልካቾች ያቀረቡት የሰውና የጽሐፍ መከላከያ ማስረጃ በተጠሪ በኩል የቀረበውን የወንጀል ክስና በተጠሪ ማስረጃ የተረጋገጠውን የወንጀል ድርጊት ለማስተባበል የማይችል መሆኑ በሥር ፍርድ ቤትና በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ተረጋግጧል። አመልካቾች ክስ ከመቅረቡ በፉት ዐቃቤ ህግ በወንጀል ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 42(1)ሀ መዝጋቱን እንደመከላከያ ያቀረቡት ቢሆንም ማስረጃ ሲገኝ ዐቃቤ ሕግ ክስ ለማቅረብ የሚከለክለው የህግ ድንጋጌ ባለመኖሩ ክስ ማቅረባችንና የሥር ፍርድ ቤትም ማስረጃችንን መዝኖ የጥፊተኝነት ውሣኔ መስጠቱ በአግባብ ነው። አመልካቾች ላልች ተከሣሾች በገደብ መለቀቃቸውን የሰበር መከራከሪያ ሃሣብ አድርገው ማቅረባቸው የህግ ድጋፍ የለውም በማለት መልስ ሰጥቷል። አመልካቾች በሰበር አቤቱታቸው ያነሷቸውን የመከራከሪያ ሃሣቦች የሚያጠናክር የመልስ መልስ በተናጠል አቅርበዋል።
ከሥር የክርክሩ አመጣጥና አመልካቾችና ተጠሪ በፅሐፍ ያደረጉት ክርክር ከላይ የተገለፀው ሲሆን እኛም ጉዲዩን መርምረናል። ጉዲዩን እንደመረመርነው የፋዳራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በአመልካቾች ላይ የሰጠውን የጥፊተኝነት ውሣኔ ይግባኝ ሰሚው የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ማጽናቱ ተገቢ ነው ወይስ አይደለም የሚለው ጭብጥ መታየት ያለበት ሆኖ አግኝተነዋል።
ይህንን ጭብጥ ለመወሰን በመጀመሪያ ፍሬ ጉዲይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ስልጣን ባላቸው ፍርድ ቤቶች ተጠሪ በማስረጃ እንዲረጋገጣቸውና አመልካቾች በመከላከያ ማስረጃ እንዲላስተባበሎቸው በመግለፅ በውሣኔቸው ያስፈሯቸውን ፍሬ ጉዲዬች አግባብነት ካላቸው የህግ ድንጋጌዎች ጋር ማገናዘብ አስፈላጊ ነው።
ተጠሪ በወንጀል ክስ ማመልከቻው በገለፀው ጊዜ ውስጥ ማለትም እንደአውሮፕውያን አቆጣጠር ከኦክቶበር 2009 ዓ.ም እስከ ዱሴንበር 2009 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በአገር ደረጃ የውጭ ምንዛሬ እጥረት የነበረ መሆን ተረጋግጧል። ይህም በመሆኑ ባንኮች በቅደም ተከተል የውጭ ምንዛሬ ለደንበኞቻቸው የሚፈቅደበትና የሚለቁበት ሥርዓት በመዘርጋት በቅደም ተከተል የማስተዲደር ኃላፉነት የነበረባቸው ቢሆንም የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) የዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያና የለገሀር ቅርንጫፍ ፣ የመርካቶ ቅርንጫፍ ፣ የአዱስ ከተማ ቅርንጫፍና የሀብተ ጊዮርጊስ ቅርንጫፍ በውጭ ምንዛሬ ለተመዘገቡ እና ተራ ለሚጠብቁ ሰዎች ሣይሰጡ ላልተመዘገቡትና የውጭ ምንዛሬ ሉፈቀድላቸው ለማይገቡ ሰዎች ጭምር የሰጡ መሆኑን ፣ በዚህም ባንኩ ለደንበኞቹ በሚሰጠው አገልግልት ላይ ችግር የተፈጠረና መልካም ስምና ዝናው የተጏዲ የባንኩም ደንበኞች የሸሹት ስለመሆኑ ከባንኩ አስተዲደር ቦርድ እና በባንኩ ከፍተኛ አክሲዮን ድርሻ ካላቸው አስር ባለሃብቶች ተወክለው ሁኔታውን ያጣሩ የተጠሪ ምስክሮች አረጋግጠዋል። ከዚህ በተጨማሪ የባንኩ ኢንስፓክሽን ክፍል ተጠሪ ባቀረበው የወንጀል ክስ በገለፀው ጊዜ ውስጥ በውጭ ምንዛሬ አጠቃቀም ፣ ፈቃድ ላይ በባንኩ ዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያና በአራቱ ቅርንጫፍች ከፍተኛ ችግር የፈፀሙና በህገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ ሉሰጣቸው የማይገባቸው ሰዎች የተሰጠ መሆኑን እንዲረጋገጡ፣ ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር የኢትዮጵያ ብሓራዊ ባንክ እንዱይዝ ከፈቀደለት በላይ ከብሓራዊ ባንክ እውቅና ውጭ የውጭ ምንዛሬ ይዞ መገኘቱና በዚህም ጥፊቱ በብሓራዊ ባንክ ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር) የተቀጣ መሆኑ ፣ ሁለተኛው አመልካች ዲንኤል ለተባለ የባንኩ ሰራተኛና ለፀሐፉው ከህግ ውጭ የውጭ ምንዛሬ የሰጠ መሆኑ ፣ ሶስተኛ አመልካች ለግል የንግድ ድርጅት ለላልች ሰዎች የተፈቀደ የውጭ ምንዛሬ ወጭ አድርጏ የሰጠ መሆኑና በዚህ ድርጊት አምስተኛው አመልካች ሙለ ተከፊይና ተባባሪ የነበረ መሆኑን ፣ አራተኛው አመልካች ለውጭ ምንዛሪ ላልተመዘገቡና ተራ ላልያዙ ሰዎች በቅድሚያ እንዱያገኙ ያደረገ መሆኑን እና የውጭ ምንዛሬ ሉፈቀድላቸው ለማይገባቸው ሰዎች የሰጠ መሆኑ ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) በለገሀር ቅርንጫፍ በመርካቶ ቅርንጫፍ ፣ በሀብተጊዮርጊስ ድልድይ ቅርንጫፍና በአዱስ ከተማ መጠኑ በርካታ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ወጭ አድርጎ ከሰጠ በኋላ የሑሳብ ምርመራ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ ያልተከፈለው መሆኑ ፣ ከላይ በዝርዝር በታዩት የሥር አመራር ጉድለት ለደረሱ ጉዲቶች አመልካቾች ኃላፉነት ያለባቸው ስለመሆኑ በተጠሪ በኩል በቀረበው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች መረጋገጡን በአመልካቾች በኩል የቀረበው የፅሐፍ የመከላከያ ማስረጃ ከላይ የተዘረዘሩት የሥራ አመራር ጉድለቶች በአመልካቾች ያልተፈፀሙ መሆናቸውን የማያሣዩ መሆኑን ፍሬ ጉዲይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ሥልጣን ባላቸው የሥር ፍ/ቤት እና ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ተረጋግጧል።
በአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ (አ.ማ) የዓለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያና በአራቱ ቅርንጫፍች የውጭ ምንዛሬ አያያዝ ፤ አጠቃቀምና አፈቃቀድ ላይ ተፈፅመዋል የተባለ ችግሮች ፍሬ ጉዲይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ስልጣን ባላቸው ፍርድ ቤቶች የተረጋገጡ ናቸው ካለን በማስከተል የሚነሣው ጥያቄ እነዚህ ችግሮች በወንጀል ህጉ በተዘረዘረው ግዙፍ ተግባር ውስጥ የሚካተቱና አመልካቾችን በወንጀል ተጠያቂ የሚያደርጉ ናቸው ወይስ አይደለም ? የሚለው ነው። ይህንን ጭብጥ ለመመለስ በመጀመሪያ በልላ ሰው ጥቅም የሥራ አመራር ላይ የተፈፀመ ጉዲት የማድረስ ወንጀል መሰረታዊ ይዘት የሚዘረዝረውን የወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 መመልከቱ አስፈላጊ ነው።
በልላ ሰው ጥቅም የሥር አመራር ላይ የተፈፀመ ጉዲት የሚል ርእስ ያለው የወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ሶስት የተለያዩ ይህንን ወንጀል የሚያቋቁሙ ሁኔታዎችን የሚደነግግ ሲሆን በወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 1 ” ማንም ሰው በሕግ ወይም በውል ግዳታ የላላን ሰው ንብረት ጥቅም እንዱጠብቅ ወይም ሥራውን እንዱመራ በሕግ ወይም በውል ግዳታ አደራ ተቀብል በተሰጠው ሃላፉነት አላግባብ በመገልገል ወይም የተጣለበትን ግዳታ ባለመፈፀም በሚጠብቀው ንብረት ጥቅም ላይ ወይም ለሚሰራበት ድርጅት በሚፈጽመው አገልግልት ላይ አስቦ ጉዲት ያደረሰ እንደሆነ ” በወንጀል ኃላፉ እንደሚሆን ይደነግጋል። የወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 2 ” ድርጊቱ በቸልተኝነት የተፈፀመ እንደሆነ ” በወንጀል ኃላፉ እንደሚሆን የሚደነግግ ሲሆን፣ የወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 3 ” ተከሣሹ ወንጀለን የፈፀመው የንብረት ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ላላ ሰው ለማስገኘት አስቦ እንደሆነ ” ለወንጀል ኃላፉ እንደሚሆን ደንግጓል። በመሰረታዊነት አንድ ሰው በልላው ሰው ጥቅም ሥራ አመራር ላይ ጉዲት የማድረስ ወንጀል ፈጽሟል ተብል በወንጀለ ኃላፉና ተጠያቂ የሚሆነው ከላይ ከዘረዘርናቸው ሶስት ሁኔታዎች አንደኛውን ወይም ሁለቱን ወይም ሁለንም ድርጊቶች ፈጽሞ ሲገኝ እንደሆነ የወንጀለን መሰረታዊ ይዘትና ባህሪ ከሚዘረዝረው የወንጀል ህግ አንቀጽ 702 ድንጋጌዎች ለመረዲት ይቻላል።
ተጠሪ በአመልካቾች ላይ የወንጀል ክስ ሲያቀርብ የጠቀሰው እና አመልካቾች ጥፊተኛ ሆነው የተገኙበት የወንጀል ህግ አንቀጽ 703 በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 7ዐ2 ከተደነገጉት 3 ድንጋጌዎች አንደኛውን በመተላለፍ ወንጀል የተፈፀመ መሆኑ ሲረጋገጥ ወንጀለ ከብድ የሚታይበትንና በኃላፉነት ሉያስጠይቅ የሚችልበትን ሁኔታ የሚዘረዝር ድንጋጌ ነው። በልላ አነጋገር የወንጀል ህግ አንቀጽ 702 የተዘረዘሩት ወንጀልች የማክበጃ ሁኔታዎችን የሚዘረዝር ድንጋጌ ሲሆን አንደኛው የማክበጃ ምክንያት አመልካቾች በተከሰሱበትና ጥፊተኛ ሆነው በተገኙበት በወንጀል ህጉ 703 ንዐስ አንቀጽ 1(ሀ) የተደነገገው ነው። የወንጀል ህጉ አንቀፅ 703 ንዐስ አንቀፅ 1/ሀ/ ቃል በቃል ሲነበብ ፣ “ወንጀለ የተፈፀመው በተሰጠው ሥልጣን ሥራውን በማከናወን ላይ በሚገኝ ፣ ወይም በተለይ ታማኝነት በተሰጠው ሞግዚት ፣ ጠበቃ ፣ ውል አዋዋይ ፣ የባንክ ሰራተኛ ፣ የንብረት አስተዲዲሪ ወይም የሑሳብ አጣሪ ወይም ሹመት ሥልጣን ባገኘ ወይም የተለየ እምነት በተጣለበት ማንኛውም ላላ ሰው የሆነ እንደሆነ ወይም የዚህ ዓይነት ተመሣሣይ ኃላፉነት በተሰጠው በማንኛውም ሰው እንደሆነ ከአስር ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራትና ከብር ሃምሣ ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጫ ይቀጣል ” የሚል ይዘት ያለው ነው።
የወንጀል ህግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1(ሀ) የሚከብደው በወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 1 የተደነገገውንና ሆነ ተብል የተሰራውን ወንጀል ወይም በወንጀል ህጉ አንቀጽ 702 ንኡስ አንቀጽ 3 ለራስ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለላላ ሰው ለማስገኘት ታስቦ የተሰራው ወይም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 2 እና ንዐስ አንቀጽ 3 የተዘረዘረውን ወንጀል ብቻ የሚያካብድ ድንጋጌ አይደለም። ድንጋጌው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 2 የተገለፀውንና በቸልተኝነት የተሰራን ወንጀል የሚያከብድ በአጠቃላይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 702 የተዘረዘሩትን ሦስት የወንጀል ድርጊት አፈፃፀሞች የሚያከብድ ድንጋጌ መሆኑ ‘’ ከባድ ሁኔታ ‘’ ከሚለው የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 703 ርዕስና ከድንጋጌው አቀራረፅና ይዘት ለመረዲት ይቻላል።
ከዚህ አንፃር ካየነው አንደኛ አመልካች የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ/አ.ማ/ ፔሬዝዲንት ሆነው ሲሰሩ በኃላፉነታቸው ማድረግ የሚገባቸውንና ጥንቃቄ ባለማድረግ፣ መውሰድ የሚገባቸውን እርምጃዎች በወቅቱ ባለመውሰድ በባንኩ ሥራ አመራር ላይ ጉዲት ያደረሱ በመሆናቸው ፣ ይህንን ተግባር ሆነ ብለው አልፈፀሙትም ቢባል እንኳን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 2/ሀ/ በቸልተኝነት የተፈፀመን ወንጀል አክብድ የሚደነግገው በመሆኑ የበታች ፍ/ቤቶች 1ኛ አመልካች በተከሰሱበት የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ ጥፊተኛ ናቸው በማለት የሰጡት ውሣኔ የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 23 የተዘረዘውን የግዙፍ ተግባር ፣ የሃሳብና የሕግ ሁኔታውን የሚያሟላና መሰረታዊ የሕግ ስህተት የላለበት ሆኖ አግኝተነዋል።
ሁለተኛ አመልካች የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ የአለም አቀፍ ባንኪንግ መምሪያ ኃላፉና የባንኩ የውጭ ምንዛሬ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆኖ ሲሰራ ያለኮሚቴው ፈቃድ በግለ የውጭ ምንዛሬ በመፍቀድ ኃላፉነቱን አላግባብ የተገለገለ መሆኑና ዲንኤል የተባለ የባንኩ ሰራተኛና በወቅቱ ፀሐፉው የነበረችውን ሴት ለመጥቀም በማሰብ አላግባብ የውጭ ምንዛሬ የፈቀደላቸው በመሆኑ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 1 እና ንዐስ አንቀጽ 3 የተዘረዘረውን ግዙፍ የወንጀል ተግባር የፈፀመና የወንጀል ሞራላዊ ሁኔታ የተሟላ በመሆኑ ይህንን ወንጀል በሚያከብደው በወንጀል ሕግ ቁጥር 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ ጥፊተኛ መባለ ተገቢ ሆኖ አግኝተነዋል።
ሶስተኛና አምስተኛ አመልካቾች የሶስተኛው አመልካች የግል ጥቅም ለማግኘት ሲል ለራሱ የንግድ ድርጅት ለላልች ሰዎች የተፈቀደ የውጭ ምንዛሬ ለሶስተኛው አመልካች የንግድ ድርጅት እንዱወስድ ማድረጋቸው ፍሬ ጉዲይ የማጣራትና ማስረጃ የመመዘን ሥልጣን ባላቸው ፍርድ ቤቶች የተረጋገጠ በመሆኑና ላልች ግድፈቶችን መፈፀማቸው ይህም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 3 የሚሸፈን በመሆኑና ይህንን ወንጀል በሚያከብደው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ ጥፊተኛ መባላቸው በአግባቡ መሆኑ አመልካች ያቀረቡትን አቤቱታ አልተቀበልነውም። አራተኛው አመልካች በመርካቶ ቅርንጫፍ የውጭ ንግድ ክፍል ኃላፉ ሆኖ ሲሰራ በውጭ ምንዛሬ አጠቃቀምና አፈቃቀድ ላይ ከፍተኛ ችግር ከፈጠሩት የባንኩ የሥራ ኃላፉዎች አንደኛው እንደነበር የተረጋገጠበት በመሆኑና ወንጀለን ሆነ ብዬ አልሰራሁትም ቢልም አድራጎቱ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 702 ንዐስ አንቀጽ 2 የሚሸፈን በመሆኑ ይህንን ወንጀል በሚያከብደው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ ጥፊተኛ መባለ በአግባቡ ሆኖ አግኝተነዋል። በአጠቃላይ ስንመለከተው አመልካቾች በተለያየ የሀሳብ ሁኔታ ወንጀለን የፈፀሙ መሆኑንና ከተለያየ የወንጀል ሃሳብ የተፈፀሙትን አድራጏቶች አጠቃልል በሚይዘውና በሚያከበደው የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ ጥፊተኛ ናቸው ተብል የተሰጠው ውሣኔ የሕጉን ድንጋጌ ይዘትና መሰረታዊ ባህሪ ያገናዘበና መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያልተፈፀመበት ነው።
አመልካቾች የሥር ፍርድ ቤት በተመሣሣይ ሁኔታ በወንጀል ተከስሰው ጥፊተኛ ሆነው የተገኙ ተከሳሾች ላይ የወሰነውን የቅጣት ውሣኔ የገደበው ሲሆን በእነሱ ላይ ቅጣቱ እንዱፈፀም የሰጠው ውሣኔ የወንጀል ሕጉን አንቀጽ 190 እና አንቀጽ 192 ድንጋጌ መሰረት ያላደረገ መሆኑን በመዘርዘር በሰበር አቤቱታቸው ተከራክረዋል። ሆኖም የሥር ፍርድ ቤት የቅጣት ውሣኔውን የገደበላቸው ተከሳሾች የቅጣት ውሣኔው ሉገደብላቸው የሚገባቸው ነበሩ ወይስ አልነበሩም በሚለው ነጥብ ተጠሪ የሰበር አመልካች ሆኖ ያልቀረበ በመሆኑ ይህ ሰበር ችልት የሚያየውና የሚመረምረው ነጥብ ሆኖ አላገኘነውም።
ሆኖም አመልካቾች የቅጣት ውሣኔው ሉገደብልን ይገባል በማለት ያቀረቡትን ክርክር በሕጉ ሰፉ ፈቅድ ሥልጣን የተሰጠው የሥር ፍርድ ቤት ያልተቀበለው በመሆኑና ይህንን መከራከሪያ ይግባኝ ሰሚው ችልት የአመልካቾችን ቅጣት ለመገደብ የሚያስችለ ሁኔታዎች ያለ መሆኑን በማረጋገጥ ውሣኔ ያልሰጡበትና በአንፃሩ የአመልካቾችን ቅጣት ሉፈፀም ይገባል በማለት የሥር ፍርድ ቤት የደረሰበትን መደምደሚያ ያፀደቀው ሆኖ አግኝተነዋል። በእኛም በኩል የቅጣቱ መፈፀም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 1 በሁለተኛው ፒራግራፍ የተቀመጠውን ግብ የሚያሳካ በመሆኑና ቅጣቱን ለመገደብ የሚያስችለ ሁኔታዎች ተሟልተዋል የሚለው ክርክር የሕግ መሰረትና ድጋፍ ያለው ሆኖ ስላላገኘነው የሥር ፍርድ ቤትና ይግባኝ ሰሚው ችልት አመልካቾች የተወሰነባቸውን የቅጣት ውሣኔ እንዱፈፅሙ የሰጡት ትዕዛዝ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያልተፈፀመበት ሆኖ አግኝተነዋል።
በአጠቃላይ የፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካቾች የወንጀል ሕግ አንቀጽ 703 ንዐስ አንቀጽ 1/ሀ/ የተደነገገውን በመተላለፍ በተለያየ የሥራ ኃላፉነት ተመድበው ሲመሩት በነበረው የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ/አ.ማ/ የሥራ አመራር ጥቅም ላይ ጉዲት የማድረስ ወንጀል የፈፀሙ ጥፊተኞች ናቸው ብል የወሰነውን የቅጣት ውሣኔ የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ማፅናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የለበትም በማለት ወስነናል።
ው ሣ ኔ
የፋዳራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትና የፋዳራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአመልካቾች ላይ የሰጡትን የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነሥርዓት ሕግ ቁጥር 195 ንዐስ አንቀጽ 2/ለ/-2 መሰረት አፅንተነዋል።
የሥር ፍርድ ቤትና ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት አንደኛ አመልካች አቶ ለይኩን ብርሃኑ ፣ ሁለተኛ አመልካች አቶ ምትኩ አበሹና አራተኛው አመልካች አቶ ቸርነት ዋጋሪ እያንዲንዲቸው በዚህ ጉዲይ እጃቸው ከተያዘበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ በአንድ ዓመት ከሶስት ወር ፅኑ እስራትና በብር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ መቀጮ እንዱቀጡ የሰጡት የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ የፀና መሆኑን አውቆ ቅጣቱን ተከታትል እንዱያስፈፅም ለክፍለ ማረሚያ ቤት ይፃፍ።
የሥር ፍርድ ቤትና ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ሶስተኛው አመልካች አቶ ጌታሁን አስማረና አምስተኛው አመልካች አቶ እንዲለ ቴኒ በዚህ ጉዲይ ተጠርጥረው እጃቸው ከተያዘበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ እያንዲንዲቸው በሁለት ዓመት ከሁለት ወር ፅኑ እስራትና በብር 15,000 /አስራ አምስት ሺህ ብር/ መቀጮ እንዱቀጡ የሰጡት የጥፊተኝነትና የቅጣት ውሣኔ የፀና መሆኑን አውቆ ቅጣቱን ተከታትል እንዱያስፈፅም ለክፍለ ማረሚያ ቤት ይፃፍ።
መዝገቡ ወደ መዝገብ ቤት ይመለስ።
No topics extracted.