No summary available.
ሰኔ 08 ቀን 2004 ዓ.ም.
ዳኞች፡- ተሻገር ገ/ሥላሴ አልማው ወላ ዓሉ መሐመድ ነጋ ደፍሳ አዲነ ንጉሴ አመልካች፡- አቶ አበራ ሁንዳ ከጠበቃ አቶ ደረጀ ኢተቻ ጋር ቀረቡ ተጠሪ፡- የፉንፍኔ የደን ደርጅት ነገረ ፈጅ አቶ ዲንኤል ኢፍ - ቀረቡ መዝገቡ የተቀጠረው ለምርመራ ሲሆን፤ መርምረን የሚከተለውን ፍርድ ሰጥተናል።
ይህ የሰበር ጉዲይ በፍርድ ቤት ውሣኔ መሰረት የተገኘን መብት መቃወም የሚቻልበትን አግባብ የሚመለከት ነው። የጉዲዩም መነሻ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካች ላይ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሱለልታ ወረዲ ፍ/ቤት ያቀረበው ክስ ነው። የክሱም ይዘት በአሁን አመልካች በአቶ አበራ ሁንዳ እና በሥር 1ኛ ተከሣሽ በነበረው የኦሮሚያ ኢንቪስትመንት ኮሚሽን መካከል ከከሣሽ ዕውቅና ውጭ በከሣሽ ይዞታ ላይ ያደረጉት ውል/ስምምነት ይፍረስልኝ በማለት የአሁን ተጠሪ የፉንፍኔ የደን ድርጅት መጠየቁን የሚያስረዲ ነው።
ተከሣሽም ቀርቦ ያነሳውን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ክርክር ፍ/ቤቱ ውድቅ ካደረገ በኋላ ከሣሽ የፉንፍኔ የደን ድርጅት በእኔ ይዞታ ላይ ግራ ቀኙ ያደረጉት ውል ይፍረስልኝ በሚል ክስ ያቅርብ እንጂ ይዞታው የእራሱ ለመሆኑ በቀጥታ የሚያስረዲ ማስረጃ አላቀረበም በኢንቨስትመንት ቢሮ አማካኝነት ለ2ኛ ተከሣሽ ለአሁን አመልካች የተሰጠው የመሬት ይዞታ የከሣሽ የፉንፍኔ ደን ድርጅት ይዞታ ለመሆኑ የሚያሳይ ካርታ የለም በልላ በኩል የፉንፍኔ የደን ድርጅት ከክሱ ጋር አያይዞ ካቀረበው የማስረጃ ዝርዝር ውስጥ 2ኛ ተከሣሽ አበራ ሁንዳ ይህንን ክርክር የተነሳበትን የመሬት ይዞታ አስመልክቶ በሰሜን ሸዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት ክስ አቅርቦ ካስወሰነ በኋላ ከኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ካርታ እንዱሰጣቸው ተብል የተወሰነ መሆኑን የሚያስረዲ ማስረጃ እንዲቀረበ ተረድቻለሁ ስለሆነም 1ኛ የመሬት ይዞታው ባለመብት ለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ባለማቅረቡና 2ኛ ክርክር ያስነሳውን የመሬት ይዞታ አበራ ሁንዳ በውሣኔ ያገኘው መሆኑን ስለተረጋገጠ በዚህ የመሬት ይዞታ ላይ ከሣሽ የፉንፍኔ የደን ድርጅት ክስ የማቅረብ መብት ያለው ሆኖ አልተገኘም በማለት ወስኗል።
በአሁን ተጠሪ በፉንፍኔ የደን ድርጅት የይግባኝ ቅሬታ አቅራቢነት መነሻ ጉዲዩን በይግባኝ የተመለከተው የኦሮሚያ ሰሜን ሸዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት በበኩለ፤ ግራ ቀኙን የሚያከራክረው የሁከት ይወገድልኝ ጉዲይ እንደሆነ ገልፆ ተከሣሽ አበራ ሁንዳ በፉንፍኔ ደን ድርጅት የመሬት ይዞታ ላይ ሁከት ፈጥሯል ወይስ አልፈጠረም? የሚለውን ጭብጥ ለመለየት እራሱ ይግባኝ ባይ ያቀረበውን ማስረጃ ተመልክቻለሁ። እንደተመለከትኩትም በጉዲዩ ላይ የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በቁጥር ከአይኦ/ፊይ/127/2001 በዐ8/03/2001 ዓ.ም የተፃፈው ደብዲቤ የሚያስረዲው አበራ ሁንዳ ለክርክሩ መነሻ በሆነው ይዞታ ላይ በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ክስ መስርቶ ክሱ የቀረበለት ፍ/ቤትም ይዞታው የአበራ ሁንዳ መሆኑን አረጋግጦ ውል እንዱፈርምና የተዘጋጀለት የይዘታ ካርታ እንዱሰጠው በወሰነው ውሣኔ መሰረት በዚህ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ታዞ ፈቃድና የመሬት ይዞታውን ማረጋገጫ ካርታ እንደሰጠ የሚያረጋግጥ ነው የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ፈቃድና የመሬት ይዞታ ካርታ ለአበራ ሁንዳ የሰጠው ኮሚሽኑ እራሱ ሳይሆን በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ውሣኔ ስለመሆኑ ከላይ እንደተገለፀው የእራሱ የከሣሹ ማስረጃ ያመለክታል። ስለሆነም በዚህ ውሣኔ ላይ ተቃውሞ ቀርቦ በይግባኝ እስካልተሻረ ድረስ ማንኛውም አካል በፍ/ቤት የተሰጠውን ውሣኔ የመፈፀም ግዳታ አለበት። አበራ ሁንዳም መሬቱን ያገኘው በፍ/ቤት ውሣኔ መሰረት ስለሆነ በፉንፍኔ ደን ድርጅት ላይ ሁከት ፈጥሯል ለማለት አይቻልም።
ይግባኝ ባይ የአሁን ተጠሪ የእራሴ የመሬቱ ይዞታ ከህግ ውጭ ተሰጥቶብኛል የሚል ከሆነ አስቀድሞ የተሰጠውን ውሣኔ ማሰረዝና የውሣኔውን ህገ-ወጥነት የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል። ይህንን አላደረገም ስለሆነም መልስ ሰጭ የነበረው የአሁን አመልካች በተጠሪ ላይ የፈጠረው ሁከት የለም በማለት የሥር የወረዲውን ፍ/ቤት ውሣኔ አፅንቶታል።
የአሁን ተጠሪ ከዚህ በላይ የተገለፀው የይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የመጨረሻ ውሣኔ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ስለሆነ ሉታረም ይገባል በማለት ላቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት በፊይል የካቲት ዐ7 ቀን 2ዐዐ3 ዓ.ም በዋለው ችልት ጉዲዩን ተመልክቶ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው መሬት በፉንፍኔ ደን ድርጅት ወሰንና ቁጥጥር ስር ያለ ስለመሆኑ ተከሣሽ ክድ ያቀረበው ክርክር ስለላለ እንዲመነ ይቆጠራል ከዚህም በቀር የይዞታ መሬቱ የፉንፍኔ ደን ድርጅት ስለመሆኑ የሚያመለክት ማስረጃ ቀርቧል።
የኢንቨስትመንት ቢሮም በፍ/ቤት ትዕዛዝ ተገድ በዚሁ መሬት ላይ ፈቃድና ካርታ ለአበራ ሁንዳ መስጠቱን እንጂ በኢንቨስትመንት ቦርድ ታይቶ የተሰጠ አለመሆኑን በፃፈው ደብዲቤ አረጋግጧል።
No specific laws extracted.
No topics extracted.
ስለሆነም የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ከአበራ ሁንዳ ጋር ተከራክሮ የተሰጠ ውሣኔ ካለ ሁለቱ ወገኖች በፈለጉት ሁኔታ ተከራክረው በተሰጠ ውሣኔ የመሬቱን ባለይዞታ ያስገድዲል የሚለው በጥርጣሬ መታየት ያለበት ጉዲይ ነው የሚለውን ሁለ መሰረት አድርጎ የኢንቨስትመንት ቢሮ እና አበራ ሁንዳ ያደረጉት ህገወጥ ውል እና የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሉሰረዝ ይገባል በማለት ወስኗል።
በዚህ ውሣኔ ላይ የአሁን አመልካች መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው በማለት ከተለያዩ የመከራከሪያ ነጥቦች አንፃር ቅሬታውን ዘርዝሮ ለዚህ የፋዳራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት የሰበር አቤቱታ በማቅረቡ ተጠሪ የፉንፍኔ ደን ድርጅት ቀርቦ የበኩለን ክርክር አቅርቧል።
እኛም ግራ ቀኙ በሰበር ደረጃ ካቀረቡት ክርክር እና በሥር በየደረጃው ከተሰጡት ውሣኔዎች አንፃር ጉዲዩን እንደተመለከትነው ግራ ቀኙን ያለያያቸው ነጥቦች ከአንድ በላይ መሆናቸውን ተገንዝበናል። ይሁን እንጂ ከእነዚህ ጭብጦች መካከል ለጉዲዩ አወሳሰን ለአንደ ቀድሞ ዕልባት መስጠት ብቻ ላላውንም ክርክር ሉያስቀር እንደሚችል በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 182/3/ እንደተደነገገው የአሁን አመልካች ክርክር ያስነሳውን መሬት በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ውሣኔ መሰረት በይዘታው ሥር የገባ መሆኑ ከተረጋገጠ የመሬቱ ባለይዞታ ነኝ የሚለው የአሁን ተጠሪ ይህንኑ ይዞታ በዲኝነት ሉያስመልስ የሚችልበት ሥርዓት ምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ በቅድሚያ ምላሽ የሚያሻው ሆኖ አግኝተነዋል።
የአሁን አመልካች በሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ. 12536 በሆነው በቀረበው ክስ መነሻ ይህንኑ ለክርክሩ መንስኤ የሆነውን የመሬት ይዞታ በሚመለከት የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ጽ/ቤት ከአመልካች ጋር ውል እንዱፈፅም፤ ፈቃድ እና ካርታም እንዱሰጥ የተወሰነበት ለመሆኑና በዚህም ውሣኔ መሰረት ውለን እንዱደረግ ፈቃድና ካርታም እንደሰጠ በየደረጃው በሶስት እርከን በተዋቀሩት ፍ/ቤቶች ውሣኔ የተረጋገጠ ጉዲይ ነው።
የአሁን ተጠሪ በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት እንዲቀረበው የሚያነሳው ክርክር እኔ በማላውቀው ውሣኔ ልገደድበት አይገባም የሚል ነው።
የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልትም የሰጠው ትንታኔ የተመረኮዘው ሁለት ተከራካሪ ወገኖች በፈለጉት አኳኋን በልላ ሰው የይዞታ መብት ላይ ተከራክረው ውሣኔ ቢያስወስኑ ይህ ውሣኔ የንብረቱን ባለይዘታ ሉያስገድደው አይችልም ህግና ደንብን ተከትል ባልተሰጠ ውሣኔ መሰረት ኢንቨስትመንት ቢሮ ተገድ የፈፀመው ውል እና የሰጠው ፈቃድ እና ካርታ ህገ ወጥ ነው። ይህ ህገ ወጥ ውል ደግሞ ሉሰረዝ ይገባል በሚለው ምክንያት ላይ ነው።
እኛም ይህንኑ የተጠሪን ክርክር እና የሰበር ሰሚው ችልት በሰጠው ፍርድ መነሻ ያደረገውን ትንታኔ ያለውን ህጋዊ መሰረት እንደሚከተለው መርምረናል።
እንደመረመርነውም በአንድ ጉዲይ በከሣሽነትና በተከሣሽነት በተሰየሙት ወገኖች መካከል ብቻ ክርክር ቢጀመር እነዚህ ወገኖች በሚከራከሩበት ጉዲይ መብት ወይም ጥቅም አለኝ የሚል ወገን ካለ ክርክር መጀመሩን እንዲተረዲ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 41 መሰረት በክርክሩ ጣልቃ በመግባት መብቱን የማስከበር መብት ያለው ስለመሆኑ የጉዲይ አመራር ፍትሃዊ እንዱሆንና በሥርዓት እንዱከናወን ለማስቻል ሲባል በተደነገገው በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕጉ ሥርዓቱ ተዘርግቷል።
ክርክሩ መጀመሩን ሳይረዲ እና ሳያውቅ ጉዲዩ በከሣሽነትና በተከሣሽነት በተሰየሙት ወገኖች መካከል የተደረገው ክርክር ተጠናቆ መወሰኑ እንኳ ቢታወቅ ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ ይረዲ ዘንድ በውሣኔው መብቴ ተነክቷል የሚለው የክርክር ተካፊይ ያልነበረው ሰው ይህንኑ ውሣኔ ለመንቀፍ፤ ለመቃወም የሚችልበትም ሥርዓት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 358 እና ተከታይ ድንጋጌ ተበጅቷል።
በዚህ ፍርደን በፈረደው ፍ/ቤት መብቱን ከማስከበር ጀምሮ ከታች ወደ ላይ በተዋቀሩት ፍ/ቤቶች አማካኝነት ይህ መሰል ተከራካሪ ወገን እርሱ የክርክር ተካፊይ ሳይሆን የተሰጠው ውሣኔ ያስከተለበትን የፍትህ መጓደል ለማረም በሚያስችል ሁኔታ የተሟላ የማስተካከያ ሥርዓት በሀገራችን የህግ ሥርዓት ተቀምጧል።
አንደ በህግ በተቋቋመ ፍ/ቤት የተሰጠው ውሣኔ በጎጊዮስ ክርክር ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በውሣኔ እስኪቋጭ ድረስ ባለው የክርክር ደረጃ የተፈፀሙት የሥነ-ሥርዓት ጉድለቶች በእራሱ በፍ/ቤቱ የሚታረሙበትን አግባብ እና ሥርዓት ካስቀመጠ እንዱሁም በውሣኔ ከተቋጨም በኋላ እንኳ ውሣኔው በእራሱ ውሣኔውን በሰጠው ፍ/ቤት እንደገና የሚታይበትን አማራጭ፤ ከዚህም በቀር እንደሁኔታው ከታች ወደ ላይ በይግባኝ አማካኝነት የተፈፀሙ የክርክር ግድፈቶች የሚታረሙበትን ሥርዓት በበቂ ሁኔታ ከዘረጋ በኋላ በዚህ በተዘረጋው ሥርዓት አለመፈፀም ወይም በዚሁ የማስተካከያ ሥርዓት አለመመራት ምን ውጤት እንደሚያስከትል በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 212 በግልፅ ተመልክቷል።
በአንድ ጉዲይ የክርክር ተካፊይ መሆን የሚገባቸው ወገኖች እነማን ናቸው? በክርክር ተካፊይ መሆን የሚገባው ሲታለፍ በምን አኳኋን መታረም እንደሚገባው ከዚህ በላይ በተጠቀሰው መሰረት አንደ በሥነ-ሥርዓት ህጉ ሽፊን የተሰጠው ጉዲይ ሆኖ ልዩ ልዩ አማራጮች ተደንግገዋል። በመሆኑም በዚህ በተደነገገው ሥርዓት መሰረት ጉዲዩ ሉመራ ያልቻለ መሆኑን የተገነዘበ ወገን ክርክሩ በመታየት ላይ እያለ ጣልቃ በመግባት፤ ከተወሰነም በኋላ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሰረት ፍርደን በፈረደው ፍ/ቤት አማካኝነት ውሣኔው ተነስቶ እንደገና በሚታይበት ሥርዓት መጠቀም እንደሚችል በህጉ ተመልክቷል። ከዚህ በቀር ሥርዓት ሳይከተለ በጉዲዩ ላይ የተሰጠው ውሣኔ የሥነ-ሥርዓት ጉድለት አለበት በማለት ብቻ ውሣኔው ዋጋ አልባ ላሆን እንደማይችል በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 212 ተደንግጓል።
ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት ክርክሮችን በዘፈቀደ ሳይሆን በሥርዓት በመምራት በአፊጣኝ እና በአነስተኛ ወጭ እንዱቋጭ ለማስቻልና የሀገሪቱ የፍ/ብሓር ፍትህ አስተዲደር ተገማች እንዱሆን ለማድረግ ታስቦ ነው። ከዚህ አንፃር አሁን የተያዘውን ጉዲይ ስንመለከት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚው ችልት በሰጠው የህግ ትርጉም ላይ ሁለቱ ተከራካሪ ወገኖች ከሣሽና ተከሣሽ በፈለጉት አኳኋን ተከራክረው የሚሰጠው ውሣኔ በክርክሩ ተሳታፉ ያልነበረን ወገን ከቶውንም ቢሆን ሉያስገድደው አይችልም በማለት የተከተለው አተረጓጏም ሥርዓት ያልተከተለ፤ ማናቸውም ክርክር በሥርዓት ሳይሆን በዘፈቀደ እንዱከራከር በር የሚከፍት ለህግ የበላይነት ተፃራሪ የሆነ አተረጓጉም በመሆኑ የህግ መሰረት ያለው ሆኖ አላገኘነውም።
ስለሆነም የአሁን አመልካች ክርክር ያስነሳውን የመሬት ይዞታ በእጁ ያደረገው በፍ/ቤት ውሣኔ መሆኑ ስለተረጋገጠ የአሁን ተጠሪ ይህ ውሣኔ መብቴን ነክቷል የሚል ከሆነ ሥርዓቱን ጠብቆ ማስለወጥ ከሚችል በቀር በዚያው ጉዲይ አዱስ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል ሥርዓት በላለበትና ይህንን ለማድረግም ተጠሪ መብት የላለው መሆኑ እየታወቀ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችልት ይህንኑ ያለ ሥርዓት የቀረበውን ክስ መነሻ አድርጎ የሰጠው ውሣኔ መሰረታዊ የሆነ የሥነ-ሥርዓታዊ ህግ ስህተት የተፈፀመበት ሆኖ ስለተገኘ የሚከተለውን ውሣኔ ሰጥተናል።
ው ሣ ኔ
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችልት በፊይል ቁጥር 1ዐ3ዐ65 በዐ7/6/2003 ዓ.ም የሰጠው ውሣኔ ተሽሯል።
ይህ ውሣኔ የአሁን ተጠሪ በዚህ የፍርድ ሐተታ እንደተገለፀው ቀደም ሲል በመ/ የተሰጠው ውሣኔ የይዞታ መብቴን ያስቀረ፤ መብቴን የነካ ነው በማለት ለመንቀፍ በሥነ - ሥርዓት ህጉ መሰረት መጠየቅና ማሳረም የሚችል ከሆነ በዚሁ ሥርዓት መሰረት ከመፈፀም በቀር በህግ በተቋቋመ ፍ/ቤት የተሰጠን ውሣኔ ላላ አዱስ ክስ በልላ ፍ/ቤት በማቅረብ ለማስለወጥ የሚያስችል መብት የለውም ብለናል።
የዚህ ሰበር ክርክር ላስከተለው ወጭና ኪሣራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻለ ብለናል።